< Return to Video

ትምህርት 1 - ከሳጥኑ ውስጥ ውጡ - ፋና ወጊው ትምህርት ቤት

  • 0:00 - 0:03
    በፋና ወጊ ትምህርት ቤታችን ወደዚህ የመጀመሪያ
    ትምህርት እንኳን በደህና መጣችሁ
  • 0:03 - 0:06
    ዛሬ ወደ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ልወስዳችሁ ነው፡፡
  • 0:06 - 0:09
    ዛሬ እያደረግን ያለው አብዛኛው
  • 0:09 - 0:15
    በእግዚአብሔር ቃል ላይ እንዳልተመሠረተ፣
    ነገር ግን በዛ ፈንታ ከብዙ ዓመታት በፊት
  • 0:15 - 0:18
    በካቶሊክ ቤተክርስቲያን በተመሠረተው ‘በኛበሰዎች’
    መሠረት ላይ እንደተመሠረተ ላሳያችሁ ነው
  • 0:18 - 0:21
    እኛም እስካሁን ድረስ በተመሳሳይ መሠረት ላይ
    እየገነባን ስለሆነ
  • 0:21 - 0:26
    እያንዳንዱ ቤተ ክርስቲያን ተመሳሳይ ይመስላል
  • 0:26 - 0:28
    እኛም ኢየሱስ ባዘዘን መንገድ ደቀመዛሙርቶችን
    በማፍራት ውጤታማ አልሆንንም፡፡
  • 0:29 - 0:33
    ያንንም ማየት ስንጀምርና አደራረጋችንን ስንቀይር
  • 0:33 - 0:36
    ደቀ መዛሙርቶችን በማፍራት እጅግ በጣም
    የበለጠ ውጤታማ እንሆናለን፡፡
  • 0:36 - 0:41
    ከአንዳንዶቹ ባህላዊ ልማዶች ሰብረን እንወጣና ወደ
  • 0:41 - 0:44
    . ኖርማሉ የክርስቲያን ህይወት ውስጥ እንመጣለን፡፡
  • 0:44 - 0:48
    ኖርማሉ(መደበኛው) የክርስቲያን ህይወት በዚህ
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የምናነበው ነው፡፡
  • 0:48 - 0:50
    በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው
    የመነቃቃት ክርስትና፡፡
  • 0:50 - 0:53
    ከኋላችን የምናየው መደበኛውን(ኖርማሉን)
    የክርስትና ህይወት አይደለም፡፡
  • 0:53 - 0:57
    መጽሐፍ ቅዱስ፣ የሐዋርያት ሥራ፣
    መደበኛው የክርስትና ሕይወት ነው፡፡
  • 0:57 - 1:01
    በዚህ የትምህርት ጊዜም ያንን እንድታዩና
    እግዚአብሔር ለናንተ ወዳዘጋጀው ሕይወት፣
  • 1:01 - 1:06
    ወደነጻነት ውስጥ የመጀመሪያውን እርምጃ
    እንድትራመዱ ልረዳችሁ ነው፡፡
  • 1:06 - 1:08
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ስለምናነበው ሕይወት፡፡
  • 1:08 - 1:11
    ስለዚህ ወደዚህ የመጀመሪያ ትምህርት
    እንኳን በደህና መጣችሁ፡፡
  • 1:11 - 1:14
    የመጨረሻው ተሐድሶ
  • 1:17 - 1:20
    የሐዋርያት ሥራ
  • 1:24 - 1:26
    ልዩነት ለማድረግ 20 ትምህርቶች
  • 1:29 - 1:32
    አዲስ ጅማሮ
  • 1:37 - 1:39
    በህይወትህ ውስጥ
  • 1:42 - 1:43
    በአንተ
  • 1:44 - 1:44
    ሕይወት
  • 1:45 - 1:46
    ውስጥ
  • 1:50 - 1:53
    ወደ ፈር ቀዳጁ ትምህርት ቤት እንኳን ደህና መጣችሁ
  • 1:54 - 1:59
    ወደዚህ ፈር ቀዳጅ ትምህርት ቤት እንኳን ደህና መጣችሁ
    ስሜ ቶርበን ሶንደርጋርድ ነው ከዴንማርክ ነኝ፡፡
  • 1:59 - 2:02
    ለናንተ የእንኳን ደህና መጣችሁ ሰላምታ በማቅረብ መቀበል
    ለኔ በጣም ታላቅ ክብር ነው፡፡
  • 2:02 - 2:06
    ይኽ ትምህርት ሕይወታችሁን እንደሚቀይር አምናለሁ፡፡
  • 2:06 - 2:10
    ብዙዎቻችሁ የኔን የዩቲዩብ ቻናል ወይም
    ዌብ ሳይት አይታችኋል
  • 2:10 - 2:11
    TheLastReformation.com
  • 2:11 - 2:15
    እናም እግዚአብሔር እያደረገ ያለውን አንዳንድ
    ምስክርነቶች ሰምታችኋል፡፡
  • 2:15 - 2:21
    ወደዚህ ህይወት ውስጥ እንድትመጡ ይህ ትምህርትም
    እንደሚረዳችሁ አምናለሁም፡፡
  • 2:21 - 2:25
    ሁላችንም በመሻት ስንጠብቀው የነበረው ሕይወት፣
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የምናነበው ሕይወት፡፡
  • 2:25 - 2:30
    እግዚአብሔር እያደረገ ያለው እጅግ በጣም አስገራሚ ነው
    ብዬ አስባለሁ በማለት አሁን መናገር እችላለሁ
  • 2:30 - 2:35
    ምክንያቱም በዚህ ትምህርት ህይወታቸው የተቀየረ ሰዎች
    ምስክርነቶች አሁን በየቀኑ እሰማለሁ፡፡
  • 2:35 - 2:39
    እኛ ደቀ መዛሙርት በምናደርግበት መንገድ
  • 2:39 - 2:42
    የተቀየሩ ሰዎች፡፡
  • 2:42 - 2:48
    የኔ ልብ ሰዎችን ማሰልጠንና ማነፅ እንደሆነ
    ከመጀመሪያው ይህን ማለት እችላለሁ፡፡
  • 2:48 - 2:53
    አምናለሁ እየሠራንበት ያለውን መንገድ፣
    እያስተማርንበት ያለውን መንገድ፣
  • 2:53 - 2:58
    ወንጌልን(የምስራቹን) እየሰበክን ያለበትን መንገድ፣
    ደቀ መዛሙርት እያፈራን ያለንበትን መንገድ በሆነ መልኩ ከቀየርን፡፡
  • 2:58 - 3:07
    አስገራሚ ነገሮች እንደሚሆኑ አምናለሁ፡፡
    ይኽም ረጅም ጊዜ መውሰድ የለበትም፡፡
  • 3:07 - 3:13
    ሰሞኑን ከጥቂት ቀናት በፊት ከሆላንድ ቪዲዮዎቼን ያየ
    የሆነ ሰው ነበር፡፡
  • 3:13 - 3:17
    እነርሱም የእረፍት ጊዜ ለማድረግ
    ወደዚህ ወደ ዴንማርክ ለመምጣት መረጡ
  • 3:17 - 3:22
    እንዲሁም እኔን ለመገናኘትና ከኔ ጋር
    በጎዳናዎች ላይ ለመውጣት፡፡
  • 3:22 - 3:27
    እኚህ አራት ልጆች ያሏቸው ጥንዶች ነበሩ
    እነርሱም ከሕፃናቶቻቸው ጋር መጡ፡፡
  • 3:27 - 3:33
    ጥቂት አወራንና እኔ ወደምኖርበት ከተማ ወረድን እነርሱም
  • 3:33 - 3:36
    ሰዎችን መፈወስ ለመማር፣
    ያንን መለማመድ ፈልገዋል፡፡
  • 3:36 - 3:38
    አንዳቸውም፡፡
  • 3:38 - 3:42
    እነርሱ ከዚህ በፊት በጎዳና ላይ ለማንም ሰው ጸልየው አያውቁም
    በጎዳና ላይም ጸልየውለት የተፈወሰ ሰው አያውቁም፡፡
  • 3:42 - 3:49
    እኔ ያደረግሁት ነገር በጣም ቀላል ነበር፣ ያን በእግዚአብሔር ቃል
    ውስጥ ታገኙታላችሁ፡፡ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡-
  • 3:49 - 3:53
    “ኑ እና ተከተሉኝ”፣
    ሰዎችም በዚያ ጊዜ ኢየሱስን ተከተሉት
  • 3:53 - 3:57
    ኢየሱስም ሰዎቹን ነካቸው፡፡
  • 3:57 - 4:01
    የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት በማድረግ አልነበረም
    ነገር ግን በእለት ተዕለት ህይወት፡፡
  • 4:01 - 4:04
    ከጥቂት ቀናት በፊት ያደረግሁትም ይኽንኑ ነው፡፡
  • 4:04 - 4:09
    “ኑ እና ተከተሉኝ” አልኩ
    እኛም ወደ ከተማው ውስጥ ወረድን
  • 4:09 - 4:16
    እርሷ ለመጀመሪያው ሰው ለመጸለይና ሲፈወስ
    20 ደቂቃ የሚጠጋ ጊዜ ወሰደባት፡፡
  • 4:16 - 4:20
    ከ20 ደቂቃዎች በኋላ ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአንድ ሰው ጸለየ
    ሰውየውም ተፈወሰ፡፡
  • 4:20 - 4:25
    ከጸለዩላቸው ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ ከአይስላንድ
    ስለነበሩ በጣም አስደናቂ ነበር፡፡
  • 4:25 - 4:29
    እነርሱ በዴንማርክ ውስጥ የሚጫወቱ
    የእግር ኳስ ቡድን አባላት ነበሩ
  • 4:29 - 4:32
    . ከእነዚያም ሰዎች አንዳንዶቹ ተፈወሱ፡፡
  • 4:32 - 4:37
    ከዚያ በኋላ ከሙሉው የእግር ኳሱ ቡድን ጋር ወደኛ መጡ
    የተጸለየላቸው 40 ሰዎችም ከኋላችን ቆመው ነበር
  • 4:37 - 4:43
    ከሆላንድ ለመጡት ለአዲሶቹ ሰዎች እንዲህ አልኩ፡-
  • 4:43 - 4:50
    “ብቻ እናንተ ጸልዩ፣ አድርጉትም፡፡”
    ከ20 እስከ 40 ደቂቃ በኋላም
  • 4:50 - 4:55
    ለተሰበሰቡ ሰዎች ቆመው እየጸለዩ ነበር
    ብዙዎቹም ሰዎች ተፈወሱ፡፡
  • 4:55 - 5:01
    በዚያ ሰዓት የተፈወሱት ሰዎች ብዛትም 30 እንደሚያህሉ አምናለሁ፡፡
  • 5:01 - 5:06
    ከጸለይንላቸው ከመጨረሻዎቹ ሁለት ሰዎች አንዱ
  • 5:06 - 5:08
    ለሁለት ዓመታት የማይግሬን ራስ ምታት ነበረበት
    እርሱም ተፈወሰ፡፡
  • 5:08 - 5:14
    ሌላኛዋ ደግሞ በመኪና አደጋ ምክንያት ለአራት አመታት
    ህመም ነበረባት
  • 5:14 - 5:19
    በሰውነቷ ውስጥም ከቦታው የወጣ አንድ አጥንት ነበረ፡፡
  • 5:19 - 5:22
    ለአራት አመታት በጀርባዋ ላይ ችግር ነበረባት
  • 5:22 - 5:27
    በጀርባዋ አካባቢም ያንን አጥንት ስትገፋው አጥንቱን ትነካው
  • 5:27 - 5:31
    ያ አጥንትም በዛ ቦታ መገኘት እንደሌለበት ማወቅ ችላ ነበር፡፡
    የሆነ ነገር ሙሉ በሙሉ ስህተት ነበር፡፡
  • 5:31 - 5:36
    ከሆላንድ ለመጣችው ሴት፣ ለሌላኛዋ እንደነገርኳት ለሷም
    “ጸልዪ ብቻ” ብዬ ነገርኳት
  • 5:36 - 5:41
    እሷም እጇን ጫነችና ጸለየች፡፡ ይኽም አጥንት ወደቦታው
    ወደ አካል ውስጥ ተመለሰ
  • 5:41 - 5:45
    ሴትየዋም የአጥንቱ ከቦታው መውጣት ከዚያ በኋላ አልተሰማትም
    እያንዳንዱም ህመም ጠፍቶ ነበር፡፡
  • 5:45 - 5:50
    ይኽን በአንድ ሰዓት ውስጥ ብቻ
    ተለማመድን (experienced this)፡፡
  • 5:50 - 5:55
    ህሙማንን መፈወስ ለመማር 40 ደቂቃ ብቻ
    ለሁለቱም ወሰደባቸው፡፡
  • 5:55 - 5:58
    ተመልሰውም ወደ ሆላንድ ሄዱ
    በዚያም ይኽንኑ እያደረጉ ነው፡፡
  • 5:58 - 6:03
    ይኽ ስለኔ አይደለም
    ይኽ በውስጣችን ስላለው ስለ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
  • 6:03 - 6:09
    ከዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቁጭ በማለት ወይም
    ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት በመሄድ
  • 6:09 - 6:13
    ስናደርገው ከነበረው ይልቅ ሰዎችን ወስዳችሁ በተለየ መልኩ
    እንዴት ደቀ መዛሙርት ማድረግ እንደምትችሉ
  • 6:13 - 6:18
    ይኽ አንድ ምሳሌ ብቻ ነው፡፡
    ይኽም ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ዓይነት ነው፣
  • 6:18 - 6:20
    አንድ ቀጥተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት
    ቤት ነው፣ ነገር ግን እጅግ የተለየ ነው
  • 6:20 - 6:23
    በኋላ ታዩታላችሁ፡፡
  • 6:23 - 6:26
    ይኽ በጣም ብዙ ቲዎሎጂ ጭንቅላታችሁ ውስጥ ማስቀመጥ
    አይደለም፡፡ ይኽ በጣም ትግበራዊ ነው
  • 6:26 - 6:33
    አሁን የምሰጣችሁ ትምህርት እጅግ ተግባራዊ ነው፡፡
    ምክንያቱም ከሆላንድ እንደመጡት ጥንዶች፣
  • 6:33 - 6:41
    ህይወታቸው ሲቀየርና በ40 ደቂቃ ውስጥ ተምረው
    ወደዚህ ወደ አዲስ ህይወት ሲመጡ አይተናል፡፡
  • 6:41 - 6:46
    ለአስር አመታት፣ ለአስራ አምስት አመታት፣ ለሃያ አመታት
    በቤተክርስቲያን ውስጥ ቁጭ ብለው
  • 6:46 - 6:52
    እንደዚህ ዓይነቱን (ይኽን) በመሻት ሲጠባበቁ የነበሩ
  • 6:52 - 6:54
    ምን ያህል ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ በዓለም አሉ?
  • 6:54 - 6:58
    ነገር ግን እነርሱ አላደረጉትም
    አሁንም ቁጭ ብለው ያስባሉ፡፡
  • 6:58 - 7:02
    እነርሱ ቁጭ ብለው ብቻ ያዳምጣሉ
    እናም አንድ ቀን ይሆናል ብለው ያስባሉ፡፡
  • 7:02 - 7:07
    ግልፅ ለመሆን (እውነቱን ለመናገር)፣
    ሁል ጊዜ ያደረግነውን ብቻ የምናደርግ ከሆነ አይሆንም፡፡
  • 7:07 - 7:12
    አይሆንም፣ ማቆም መድፈር አለብን ራሳችንንም
    ምን እያደረግን እንደሆነ መጠየቅ መድፈር አለብን፡፡
  • 7:12 - 7:14
    እያደረግን ያለው የእግዚአብሔር ቃል ነውን?
  • 7:14 - 7:16
    ደቀ መዛሙርት በእርግጥ እየፈጠርን ነው?
  • 7:16 - 7:21
    ከፊት ለፊቱ የቆምነው መነቃቃት (the revival)፣
    የመጨረሻው ተሐድሶ ነው፡፡
  • 7:21 - 7:24
    ደቀ መዛሙርቶችን ስለመፍጠር(ሰለማፍራት)
    የሆነ ተሐድሶ ነው፡፡
  • 7:25 - 7:32
    ምክንያቱም እግዚአብሔር ደቀ መዛሙርት እንድናፈራ
    የሰጠንን መሣሪያዎች በድጋሜ ከተጠቀምን
  • 7:32 - 7:34
    ልክ ኢየሱስ ይኽን እንድንሠራ እንደጠራን፡፡
  • 7:34 - 7:37
    እርሱ እንድናደርገው ባዘዘን መንገድም አድርጉት፡፡
  • 7:37 - 7:43
    በጣም ብዙ ሲሆን ማየት እንችላለን፣
    ምናልባትም እድሜ ዘመናቸውን በሙሉ
  • 7:43 - 7:47
    ቤተክርስቲያን ውስጥ ተቀምጠው የነበሩ
    የብዙ ሰዎች ምስክርነቶች አሉኝ፡፡
  • 7:47 - 7:53
    ወይም ለ20 ወይም ለ40 ዓመታት
    ማንንም ወደ ክርስቶስ ያልመሩ፣
  • 7:53 - 7:55
    በሽተኛን ፈውሰው የማያውቁ፣
    አንድንም ጋኔን አስወጥተው የማያውቁ፣
  • 7:55 - 8:01
    ከተፈጥሮ በላይ የሆነውን ህይወት
    ተለማምደው በፍፁም የማያውቁና
  • 8:01 - 8:04
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ እንደምናነበው
    ምስክርነቶች የሎሏቸው፡፡
  • 8:04 - 8:09
    ነገር ግን ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዓታት
    ከእነርሱ ጋር በመሥራት፣ ምናልባት አንድ ቀን
  • 8:09 - 8:15
    ህይወታቸው ይቀየርና ከዛ በኋላ እነርሱ
    ይኽን አዲስ ህይወት መኖር ይቀጥላሉ፡፡
  • 8:15 - 8:20
    በፊት፣ የነርሱ ህይወት በሐዋርያት ሥራ ውስጥ እንደምናነበው
    አይመስልም ነበር፡፡
  • 8:20 - 8:26
    ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ግን ህይወታቸው በሐዋርያት ሥራ
    ውስጥ እንደምናነበው መምሰል ጀመረ፡፡
  • 8:26 - 8:30
    በኋላ ላይ በዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ጊዜ
    ያን የሚመስሉ
  • 8:30 - 8:32
    በጣም ብዙ ምስክርነቶች እናገራለሁ፡፡
  • 8:32 - 8:36
    እናንተም በእግዚአብሔር ጥቅም ላይ ለመዋል
    በመሻት እየተጠባበቃችሁ ከሆነ፣
  • 8:36 - 8:42
    እግዚአብሔር እንዴት እንደሚጠቀምባችሁ በትግበራ ለማወቅ
    አጥብቃችሁ የምትሹ ከሆነ፡፡
  • 8:42 - 8:44
    ከሆነ ወደ ትክክለኛው ቦታ መጥታችኋል፡፡
  • 8:44 - 8:49
    ቲዖሎጂ ብቻ ከፈለጋችሁና ነገሮችን ብቻ
    መወያየት(መነጋገር) ከፈለጋችሁ ከዛ
  • 8:49 - 8:51
    ይህ ለናንተ የሚሆን የመጽሐፍ ቅዱስ
    ትምህርት ቤት አይደለም፡፡
  • 8:51 - 8:58
    ምክንያቱም ይኽ ስለ ትክክለኛው ቲዖሎጂ ብቻ
    እንዳልሆነ ማወቅ አለብን፡፡
  • 8:58 - 8:59
    ያንን እዚህ ልታዩት ነው፡፡
  • 8:59 - 9:04
    በእርግጥ ነገሮችን በቀላል መንገድ ስለማድረግ ነው፣
    ኢየሱስ ባደረገበት መንገድ፡፡
  • 9:04 - 9:11
    ዓይኖቻችንን ስለመክፈትና ሃይማኖታዊ መነፅሮቻችንን
    ስለማውለቅ እናም
  • 9:11 - 9:14
    ከመጀመሪያው ስለመጀመር ነው፡፡
  • 9:14 - 9:16
    በዚህ በመጀመሪያው ትምህርት የማደርገው:
  • 9:16 - 9:19
    በአንዳንድ የቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ
    ልወስዳችሁ ነው፡፡
  • 9:19 - 9:23
    ብዙ ነገሮች በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ
    አጓጊ አይደሉም ነገር ግን ይኽ
  • 9:23 - 9:31
    አጓጊ ነው ምክንያቱም ነገሮች ዛሬ ያሉበት መንገድ ለምን
    እንደሆኑ ይኽ ሊያሳያችሁ ስለሆነ ነው፡፡
  • 9:31 - 9:35
    እና በዓለም ውስጥ ያሉት ቤተክርስቲያኖች
    ዛሬ እንዴት እንደሆኑ፡፡
  • 9:35 - 9:41
    ከእነዚያ ባሕሎች ውስጥ ሰብራችሁ እንድትወጡና
    አጥብቃችሁ ስትሹት ወደነበረው
  • 9:41 - 9:43
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ወዳነበብነው ሕይወት
    እንድትመጡ ይረዳችኋል፡፡
  • 9:43 - 9:47
    እዚህ መጽሐፍ ቅዱስ እንዳለኝ አስቀድሜ
    መናገር እፈልጋለሁ፡፡
  • 9:47 - 9:56
    አንድ ክርስቲያን እንዴት መኖር እንዳለበትና ኖርማሉ(መደበኛው)
    የክርስትና ሕይወት ምን እንደሆነ ማየት ከፈለግሁ፡፡
  • 9:56 - 10:01
    ያን የት ነው መፈለግ ያለብኝ?
    ብሉይ ኪዳን ውስጥ መፈለግ አለብኝ?
  • 10:01 - 10:07
    አይደለም፣ ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደናንተና እነደኔ
    የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የሆነ ክርስቲያን አታገኙም፡፡
  • 10:07 - 10:14
    ብሉይ ኪዳን ከኢየሱስ በፊት ነበረ፣
    ያረጀው (the old) ኪዳን(ስምምነት) ነበረ እናም
  • 10:14 - 10:19
    በዚያን ጊዜ የነበሩት ነገሮች አሁን ካሉት
    በጣም የተለዩ ነበሩ፡፡
  • 10:19 - 10:21
    ነገር ግን ዛሬ ብዙ ቤተክርስቲያኖች እና
    ብዙ ክርስቲያኖች
  • 10:21 - 10:26
    አሁንም ብሉይ ኪዳን (አሮጌው ስምምነት) ውስጥና በአሮጌው
    ስምምነት የአዕምሮ-ትኩረት (mind-set) ውስጥ ይኖራሉ፡፡
  • 10:26 - 10:32
    ነገር ግን ደቀ መዝሙር ምን ማለት እንደሆነ የምናገኘው
    በብሉይ ኪዳን ውስጥ አይደለም፡፡
  • 10:32 - 10:34
    ታዲያ የት ነው የማገኘው?
  • 10:34 - 10:39
    በአራቱ ወንጌላት ውስጥ ነውን? አይደለም፣ አይደለም
    በአራቱ ወንጌላት ውስጥ አይደለም፡፡
  • 10:39 - 10:45
    በእርግጥ አራቱ የምሥራቾች፣ ኢየሱስ ምን እንድናደርግ
    እንደጠራን የምታዩበት፣
  • 10:45 - 10:49
    የኢየሱስ ቃላት ናቸው፡፡ እና የእርሱን ደቀ መዛሙርት
    እንዴት እንደላካቸው፣
  • 10:49 - 10:52
    ኢየሱስ እንዴት ይኖርና ይሠራ እንደነበርና እርሱ
    በመስቀል ላይ እንዴት እንደሞተና በድጋሜ እንደተነሣ፡፡
  • 10:52 - 10:58
    በአራቱ የምስራቾች ውስጥ ግን እንዳንተና(ቺና) እንደኔ
    ደቀመዛሙርት አታይም(ዪም)፣ ለምን?
  • 10:58 - 11:02
    ምክንያቱም በወንጌላቱ ውስጥ ዛሬ እኛ በምንጠመቅበት መንገድ
    ማንም ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ አልተጠመቀም፡፡
  • 11:02 - 11:07
    እኛ ዛሬ በምንቀበልበት መንገድ
    ማንም መንፈስ ቅዱስን አልተቀበለም፣
  • 11:07 - 11:13
    ምክንያቱም በአራቱ ወንጌላት (መልካም ዜናዎች) ውስጥ
    መንፈስ ቅዱስ አልወረደም ነበርና፡፡
  • 11:13 - 11:16
    በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ገና አልሞተም ነበርና
    ከሞትም ገና አልተነሣም ነበርና፡፡
  • 11:16 - 11:20
    አራቱ ወንጌላት አሁንም ገና ብሉይ ኪዳን ናቸው፡፡
  • 11:20 - 11:26
    ዛሬ ብዙ ክርስቲያኖችም ደግሞ
    በአራቱ ወንጌላት ውስጥ ይኖራሉ
  • 11:26 - 11:30
    እዚያም መኖር እንደሌለብን አልተረዱምም፡፡
    ከወንጌላቱ ቀጥሎ በሚገኘው መጽሐፍ፣
  • 11:30 - 11:33
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ እንደምናነበው መኖር አለብን፡፡
    ምክንያቱም በሐዋርያት ሥራ ውስጥ
  • 11:33 - 11:37
    መንፈስ ቅዱስ እንዴት በሰዎች ላይ
    እንደወረደ እናነባለን
  • 11:37 - 11:42
    ሰዎቹም እንዴት መኖር እንደጀመሩ ያሳያል፡፡
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ምን ታነባለህ(ታነቢያለሽ)?
  • 11:42 - 11:47
    እግዚአብሔርን ስላፈቀሩ፣ ኢየሱስን ስላፈቀሩ፣
    መስቀሉን ተሸክመው
  • 11:47 - 11:51
    እርሱን ለመከተል ስለፈቀዱ ሰዎች ታነባለህ፣
    ብዙዎቹም ሰማእት ሆነው ሞቱ፡፡
  • 11:51 - 11:55
    መንፈስ ቅዱስ እንዴት በእነርሱ ይሠራ
    እንደነበርም ደግሞ ታነቢያለሽ፡፡
  • 11:55 - 12:02
    መንፈስ ቅዱስ እነርሱን እንዴት ይመራቸው እንደነበር፣ የእርሱን
    ቤተክርስቲያን ለመገንባት እግዚአብሔር እንዴት
  • 12:02 - 12:05
    እንደተጠቀማቸው ታነባለህ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ሥራ
    መጽሐፍ ውስጥ በሙሉ እየሠራ ነበር
  • 12:05 - 12:11
    መንፈስ ቅዱስ እንዴት በሕልም እንደመራቸው፣
    እነርሱን እንዴት እንደተናገራቸው
  • 12:11 - 12:16
    እነርሱም እንዴት እንደተናገሩ በሽተኞችንም እንዴት እንደፈወሱና
    አጋንንትን እንዳስወጡ ታያላችሁ፡፡
  • 12:16 - 12:20
    ይኽን ነው በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የምናነበው፡፡
  • 12:20 - 12:25
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
    መደበኛው የክርስቲያን ሕይወት ነው፡፡
  • 12:25 - 12:32
    ቤተክርስቲያናችሁ ውስጥ ቁጭ ብላችሁ ዙሪያውን ከምታዩበት
    ከቤተክርስቲያን ድባብ ከመጣችሁ፣
  • 12:32 - 12:38
    የምታዩትም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ
    ከምታነቡት በጣም ከተለየባችሁ፡፡
  • 12:38 - 12:46
    በዙሪያችሁ የምታዩት መደበኛው የክርስትና ሕይወት እንዳልሆነ
    ልነግራችሁ እፈልጋለሁ፡፡
  • 12:46 - 12:48
    እንዲህ አይደለም መሆን ያለበት፡፡
  • 12:48 - 12:52
    በዚያ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ እንደምናነበው ነው
    መሆን ያለበት፡፡
  • 12:52 - 12:55
    በአንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ፣ በአንድ የእምነት ወገን ውስጥ
    ተቀምጣችሁ ዙሪያውን እየተመለከታችሁ ከሆነ፣
  • 12:55 - 13:00
    ክርስቲያን መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ አንድ ስዕል(እይታ)
    ብቻ ነው የምታገኙት፡፡
  • 13:00 - 13:03
    በሌላ ቤተክርስቲያን፣ በሌላ የእምነት ወገን ውስጥ
    ከሆናችሁ ግን፣
  • 13:03 - 13:07
    ያኔ ክርስቲያን መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ
    የተለየ ዕይታ ታገኛላችሁ፡፡
  • 13:07 - 13:13
    ነገር ግን መቆም አለብን፣ ቃሉንም ብቻ፣ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን
    መውሰድ አለብን፡፡
  • 13:13 - 13:18
    በተለይ ደቀመዝሙር መሆን ማለት ምን ማለት ነው እና
    እንዴት መኖር አለብን ወደሚል ሲመጣ፡፡
  • 13:18 - 13:26
    ይኽ ዛሬም ያው ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ትናንትና፣ ዛሬ፣
    እስከለዘላለምም ያው እንደሆነ እያንዳንዱ ሰው ያምናል፡፡
  • 13:26 - 13:31
    እርሱ አልተቀየረም፡፡ ወደ መዳን (ድኅነት) ስንመጣ
    ያንን እናምናለን፡፡
  • 13:31 - 13:35
    ወደ ብዙ ሌሎች ነገሮችም ስንመጣ
    ያንን እናምናለን፡፡
  • 13:35 - 13:40
    ስለ ሕይወቱስ ግን? ስለ መንፈስ ቅዱስስ?
    ስለ ተአምራቱስ?
  • 13:40 - 13:45
    እርሱ ካልተቀየረ፣ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ
    የምናነበው ዛሬም ያው ነው፡፡
  • 13:45 - 13:48
    ምክንያቱም እርሱ ካልተቀየረ
    መንፈስ ቅዱስም አልተቀየረም፡፡
  • 13:48 - 13:51
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
    አብዝቶ ስለ ሐዋርያቱ አይደለም፡፡
  • 13:51 - 13:55
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ መንፈስ ቅዱስ በመጀመሪያዎቹ
    ደቀመዛሙርት ውስጥ ሆኖ እንደሠራና
  • 13:55 - 14:01
    እነርሱ እንዴት ይኖሩ እንደነበር በኋላ ላይ ልታዩት ነው፡፡
    እርሱ አልተቀየረም፡፡
  • 14:01 - 14:06
    መንፈስ ቅዱስ አልተቀየረም ስለዚህ ዛሬ የኛ ሕይወት እንደ
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ መሆን አለበት፡፡
  • 14:06 - 14:12
    ያን ማየት ስጀምር፣ በዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ውስጥ
    የማካፍላችሁ አንዳንድ ነገሮች፣
  • 14:12 - 14:19
    በዚያን ጊዜ እኔ ራሴ ከመደበኛው ህይወቴ
    ሰበሬ መውጣት
  • 14:19 - 14:21
    ጀምሬ ነበር፡፡
  • 14:21 - 14:26
    አንድ እርምጃ ተራመድኩ፣ ከዚያም አንድ ተጨማሪ ርምጃ፣
    በድንገትም እዚያ እንደምናነበው
  • 14:26 - 14:34
    ብዙ በጣም ብዙ ሕይወት ማየት ጀመርሁ፡፡
    እግዚአብሔር እኔን እንዴት
  • 14:34 - 14:41
    በሕልሞች እንደመራኝና በመንፈስ ቅዱስ እየመራኝ እንዴት
    ሲናገረኝ እንደነበረ ብዙ አስደናቂ ምስክርነቶች አሉኝ፡፡
  • 14:41 - 14:45
    ብዙ ሰዎች ሲድኑና በመንፈስ ቅዱስ ሲሞሉ
    አይቻለሁ፡፡
  • 14:45 - 14:48
    ጸልዬላቸው ወዲያውኑም መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ላይ
    ሲመጣ አይቻለሁ፡፡
  • 14:48 - 14:52
    ሰዎች በልሳኖች መጸለይ ሲጀምሩ
    ሰዎችም ከአጋንንት ነጻ ሲወጡ አይቻለሁ፡፡
  • 14:52 - 15:00
    ይኽ ለኔ መደበኛ ሕይወት መሆን እየጀመረ ነው
    ብዙዎቻችሁም
  • 15:00 - 15:06
    ስለዚህ ሕይወት ሰምታችኋል፡፡ በተደጋጋሚ ግን ስለዚህ ሕይወት
    በቻይና ወይም በአፍሪካ
  • 15:06 - 15:09
    በሌሎች አገሮችም ሰምተናል፣ ነገር ግን ምዕራቡስ?
  • 15:09 - 15:12
    እኔ በዴንማርክ ነው እየኖርኩ ያለሁት፣
    ምዕራባዊ ሀገር ነው፡፡
  • 15:12 - 15:18
    ኢየሱስም እዚህ በምዕራብ ያው ነው፣
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ እንደምናነበው፡፡
  • 15:18 - 15:22
    በቻይና ውስጥ ስላለው የምንሰማቸው ታሪኮች
    እዚህም ማየት እንችላለን፣ ለምን?
  • 15:22 - 15:24
    ምክንያቱም ኢየሱስ እዚህም ያው ነው፡፡
  • 15:24 - 15:29
    እያነሣሣ ሊቀሰቅሳችሁ ስለሆነ ይኽን ትምህርት ለመቀበል
    ዝግጁ እንደሆናችሁ
  • 15:29 - 15:30
    ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
  • 15:30 - 15:34
    ከመጀመሪያው ይኽን ማለት እፈልጋለሁ፣
    እግዚአብሔር ስጦታ ሰጥቶኛል ስጦታዬም
  • 15:34 - 15:40
    ሰዎችን በማነሣሣት መቀስቀስ ነው፡፡
  • 15:40 - 15:41
    እናንተን በማነሣሣት መቀስቀስ እፈልጋለሁ፡፡
  • 15:41 - 15:46
    ከዚህ በፊት ፈፅሞ ያልሰማችሁትን የሆነ ነገር ማለትና
    የሆነ ነገር ላሳያችሁ እፈልጋለሁ፡፡
  • 15:46 - 15:54
    ስትሰሙትና አዲስ ሲሆን፣ በቃ አቁሙና
    በልባችሁ አስቡ ይሰማችሁም
  • 15:54 - 15:58
    ወደ እግዚአብሔር ቃል ውስጥም ተመልከቱ፡፡
    እያልኩ ያለሁት እውነት (ትክክል) ነውን?
  • 15:58 - 16:04
    እስከዛሬ ስታደርጉት የነበረው ባህሎችን እንጂ
  • 16:04 - 16:07
    የእግዚአብሔርን ቃል ስላልነበረ ትደነግጣላችሁ፡
  • 16:07 - 16:11
    ወደ አንዳንድ የቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ልወስዳችሁና
  • 16:11 - 16:17
    ምን መሠረት ላይ እየገነባን እንደሆነ ላሳያችሁ ነው፣
  • 16:17 - 16:22
    ከዚህም ሰብራችሁ እንድትወጡ የእውነት በጣም ትልቅ
    ረዳት ይሆንላችኋል፡፡
  • 16:22 - 16:26
    በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ጊዜ
    መልሼ መላልሼ እመጣለሁ፡፡
  • 16:26 - 16:31
    ኢየሱስ እያለ ያለውን እንድትቀበሉ
    ይኽ ትምህርት ይረዳችኋል፡፡
  • 16:33 - 16:35
    ለዛ ዝግጁ ነህ? ለዛ ዝግጁ ነሽ?
  • 16:37 - 16:43
    በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው
    የተነቃቃ ክርስትና፣ የሐዋርያት ሥራ፡፡
  • 16:43 - 16:47
    የሐዋርያት ሥራ መደበኛው(ኖርማሉ)
    የክርስትና ሕይወት ነው፡፡
  • 16:48 - 16:52
    በሰዎች ላይ ከፈሰሰው ከመንፈስ ቅዱስ እና
  • 16:52 - 16:54
    የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት እንዴት ይኖሩ
    እንደነበር ይጀምራል፡፡
  • 16:54 - 16:58
    በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ጊዜ በሐዋርያት ሥራ
    መጽሐፍ ውስጥ እሄዳለሁ እናንተም
  • 16:58 - 17:00
    በጣም ብዙ ነገሮች ታያላችሁ፡፡
  • 17:01 - 17:05
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ዓለምን ስለቀየሩ
    በእነርሱ መንፈስ ቅዱስ ስለጀመረባቸው
  • 17:05 - 17:10
    ስለጥቂት ሰዎች ነው ይህም
    በመላው ዓለም ተፅእኖ አመጣ፡፡
  • 17:11 - 17:13
    በመጀመሪያው የተነቃቃ ክርስትና ነበረን፡፡
  • 17:13 - 17:17
    በተጨማሪም የሰማዕትነት ክርስትና፡፡
    ብዙ ሰዎች ለእምነታቸው ሞተዋል፡፡
  • 17:19 - 17:24
    ከዛ የሆነ ነገር ተከሰተ፡፡
    በ300 ዓመተ ምህረት አካባቢ
  • 17:24 - 17:29
    በክርስትና ውስጥ በጣም ብዙ ነገሮችን የቀየረ
    ቆስጠንጢኖስ የሚባል አንድ ገዢ ነበረ፡፡
  • 17:29 - 17:36
    ከእሱ በፊት ክርስትና ተሰቃይቶ ነበር
    ብዙዎችም ሞቱ፣
  • 17:36 - 17:44
    ገዢው ቆስጠንጢኖስ ግን ክርስትናን ወሰደና
    ከክርስትና ውስጥ ብሔራዊ ሃይማኖት ፈጠረ፡፡
  • 17:44 - 17:52
    ብዙ ክርስቲያኖች ቆስጠንጢኖስ በቤተክርስቲያን ውስጥ
    ጥሩ ሥራ የሠራ ክርስቲያን ነበር ብለው ያምናሉ፣
  • 17:52 - 17:56
    በእውነታው ግን ለመልካም ቤተክርስቲያንን አመሰቃቀላት፡፡
  • 17:56 - 18:05
    ምክንያቱም እኛ ዛሬም እስካሁን እየገነባንባቸው ያለናቸውን
    ብዙ ነገሮች እሱ በጊዜው ቀየራቸው፡፡
  • 18:05 - 18:14
    ከቆስጠንጢኖስ ውስጥም
    የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን አገኘን፡፡
  • 18:14 - 18:18
    ነገር ግን ዋጋ ነበረው ምክንያቱም
    ብዙ ነገሮች ተቀይረዋል፡፡
  • 18:18 - 18:23
    አሁን ለናንተ: “የካቶሊክ ቤተክርስቲያን፣ ስለ ቤተክርስቲያኑ
    ሰዎች ምንድን ነው የሚያስቡት?” ብላችሁ
  • 18:23 - 18:27
    በጣም፣ በጣም ትልቅ የቤተክርስቲያን ሕንፃ ነው
    ሰዎች የሚያስቡት፣
  • 18:27 - 18:33
    ሰዎች ጳጳሱን ያስባሉ፣ ካህኑን ያስባሉ፣
    ቅዳሴንና እሁድ የሚደረገውን
  • 18:33 - 18:35
    የቤተክርስቲያን ስብሰባዎች ያስባሉ፡፡
  • 18:35 - 18:40
    በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዙሪያ ስላለ
    አጠቃላይ ቅንብር ያስባሉ፡፡
  • 18:42 - 18:45
    ነገር ግን ይህን ሁሉ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ
    የት ነው የምታገኙት?
  • 18:46 - 18:48
    ጳጳሱን የት ነው የምታገኙት?
    [በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ]
  • 18:48 - 18:51
    እኛ [አሁን]በምናየው መንገድ፣ ካህን የት ነው የምታገኙት?
    [በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ]
  • 18:51 - 18:53
    የቤተክርስቲያን ስብሰባን የት ነው የምታገኙት?
    [በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ]
  • 18:54 - 19:00
    የቤተክርስቲያን ሕንጻን የት ነው የምታገኙት?
    እሁድ የሚደረገውን ስብስብ የት ነው የምታገኙት?
  • 19:00 - 19:08
    ያን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ አታገኙም፡፡
    ኢየሱስ የመጣው መቅደሱን አፍርሶ
  • 19:08 - 19:13
    መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ መኖር የሚችልበት በሕያው ድንጋዮች
    የተሠራ አንድ አዲስ መቅደስ ሊገነባ ነው፡፡
  • 19:14 - 19:20
    ኢየሱስም መጣና እንዲህ አለ፡-
    “ማንንም አባቴ ብላችሁ አትጥሩ ምክንያቱም
  • 19:20 - 19:22
    አባታችሁ አንዱ ነውና፣ እርሱም
    በሰማይ ያለው እግዚአብሔር፡፡”
  • 19:22 - 19:28
    ኢየሱስ ከብዙ ነገሮች ጋር መጣ
    የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ግን ቀየረቻቸው፡፡
  • 19:28 - 19:33
    ቅዱሱን ቦታ አገኘን፣ መቅደሱን አገኘን
    ጳጳሱንም አገኘን፡፡
  • 19:33 - 19:40
    ጳጳስ የሚለው ቃል የመጣው አባት ከሚለው ቃል ነው፣
    እና ዛሬ በዓለም ዙሪያ
  • 19:40 - 19:46
    “ኦህ፣ ጳጳሱ፣ አባታችን” የሚሉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
  • 19:46 - 19:48
    ያ ግን ኢየሱስ ይዞት የመጣው አልረነበረም፡፡
  • 19:49 - 19:56
    ብዙ ነገሮች ተቀይረዋል ማለት እፈልጋለሁ፡፡
    ቅያሬውን ከተመለከትንም፣
  • 19:56 - 19:59
    ከየት ነው ቅያሬዎቹ የመጡት?
  • 20:00 - 20:07
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ አይሁዶች ነበሩ፣
    አይሁዶች ቅዱስ ቀናቸው ቅዳሜ እለት ነበር፡፡
  • 20:08 - 20:13
    ኢየሱስ መጣ፣ ለእርሱ ከሌላው ቀን የበለጠ ቅዱስ
    የሆነ ቀን አልነበረውም፡፡
  • 20:13 - 20:17
    አሁን በኢየሱስ ክርስቶስ ማግኘት የምንችለው እረፍት አለ
    በሌላ ጊዜ በዚህ ርእስ ላይ
  • 20:17 - 20:19
    አንዳንድ ትምህርት ይኖራል፡፡
  • 20:20 - 20:27
    ኢየሱስ አዲስ ከሆነ ነገር ጋር መጣ ከዚያ በኋላ ግን
    የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መጣች እነሱም
  • 20:27 - 20:33
    አንድ ትልቅ ሃይማኖት መገንባት ፈለጉና
    ኢየሱስ የጀመረውን ብዙ ነገሮች ቀየሩ፡፡
  • 20:33 - 20:38
    ስለዚህ እነሱ አዲስ [የረፍት] ቀን ፈጠሩ፣
    እሁድ፡፡ ለምን?
  • 20:38 - 20:44
    ምክንያቱም እሁድ የፀሐይ ቀን ነበረ፡፡
    የ ፀሐይ-አምላክ ቀን The Sun-god's day፡፡
  • 20:44 - 20:53
    ምክንያቱም ቆስጠንጢኖስ ፀሐይ-አምላክ አምልኮ ውስጥ
    ሊቀ ካህን ነበረ
  • 20:53 - 21:00
    ሊቀ ካህን መሆኑንም እስከ ሚሞትበት ቀን ድረስ ቀጠለ፡፡
    ፀሐይ-አምላክ ን በማምለክ በጣም ብዙ ነገሮች አድርጓል፡፡
  • 21:00 - 21:09
    ይህን መሠረት ወሰደ፡፡ በድንገትም እሁድን አገኘን፣
    ቅዱስ ቀን፡፡ ለምን?
  • 21:09 - 21:14
    በቆስጠንጢኖስ ምክንያትና ፀሐይ አምላክ
    ተብላ ስለምትመለክ፡፡
  • 21:14 - 21:21
    እሱ አንድ መቅደስም ገንብቷል መቅደሱንም
    ወደ ምስራቅ አዙሮታል፡፡
  • 21:21 - 21:26
    ስለዚህ እሱ ያስቀመጠው ካህን፣
    ፀሐይን በጭንቅላቱ ላይ አገኘ፡፡
  • 21:26 - 21:30
    ለዚያ ነው፣ በዛው ሰአት ላይ፣ እሱ በሆነ መንገድ
    ፀሐይ-አምላክ ን ያመልካል፡፡
  • 21:31 - 21:35
    እዚያ ከምናየው ጋር ሲነፃፀር ዛሬ ባለችው
    የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ
  • 21:37 - 21:42
    ብዙ ነገሮች ተቀይረዋል፡፡
    ያ ቅያሬም ዋጋ ነበረው [አስከፍሏል]፡፡
  • 21:42 - 21:49
    ይህን ማለት እችላለሁ፣ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ
    ጴጥሮስና ዮሐንስን የምታዩበት አንድ ምስክርነት ነበረ፣
  • 21:49 - 21:54
    ለመጸለይ እየሄዱ ነበረ በዚያም ምጽዋት እየለመነ
    የነበረ አንድ አንካሳ (ሽባ) ሰው ነበረ፡፡
  • 21:54 - 21:59
    አንካሳውንም ሰውዬ ተመለከቱትና እንዲህ አሉት፣
    “ብርና ወርቅ የለንም፤
  • 21:59 - 22:03
    ይህን ያለንን ግን እንሰጥሃለን፤ በኢየሱስ ስም ተነሣ።”
  • 22:03 - 22:10
    እነርሱም ሽባውን ሰውዬ አስነሡት እርሱም ተፈወሰ፡፡
    ያን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ሁሉ ታያላችሁ፡፡
  • 22:10 - 22:17
    ነገር ግን በዚያ ጊዜ ያ ተቀየረ፡፡
    ዛሬ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ አንድ ካህን:
  • 22:17 - 22:21
    “ወርቅና ብር የለንም” ሊል ይችላል?፡፡
    አይችልም! ለምን? ምክንያቱም እነሱ ብዙ
  • 22:21 - 22:26
    ወርቅ አላቸው፣ ብዙ ብር አላቸው፡፡
    ምክንያቱም አሁን አንድ ትልቅ ድርጅት፣
  • 22:26 - 22:29
    አንድ ትልቅ ማሽን፣
    አንድ ትልቅ ካምፓኒ ሆኗል፡፡
  • 22:31 - 22:35
    ስለዚህ ብርና ወርቅ የለንም ማለት አይችሉም፣
    በኢየሱስ ስም ተነሣ! ማለትም ግን ደግሞ አይችሉም፡፡
  • 22:35 - 22:42
    ለምን? ምክንያቱም
    መንፈስ ቅዱስ ነጻ መሆን ይፈልጋል፡፡
  • 22:42 - 22:48
    እግዚአብሔር ባህሎቻችንን መባረኪያ ወይም
    ማረጋገጫ መሆን አይፈልግም፡፡
  • 22:48 - 22:51
    እርሱ (የራሱን)ቃሉን ማረጋገጥና
    መባረክ ነው የሚፈልገው፡፡
  • 22:51 - 22:56
    በጣም ብዙ ነገሮችን መቀየር ስንጀምርና ከቃሉ ውስጥ
    ሃይማኖት መሥራት ስንጀምር
  • 22:56 - 23:02
    እግዚአብሔርንም ሳጥን ውስጥ ማስቀመጥ ስንጀምር፣
    ከዛ ምን ይሆናል? መንፈስ ቅዱስ ይሄዳል፡፡
  • 23:02 - 23:05
    ኃይሉም [ትቶ] ይሄዳል፣
    ሕይወትም [ትቶ] ይሄዳል፡፡
  • 23:05 - 23:10
    ለምን? ምክንያቱም በእግዚአብሔር ቃል ላይ ያልሆነ
    መሠረት ስለገነባን፡፡
  • 23:10 - 23:15
    ነገር ግን ከዚህ ሲስተም ውስጥ
    ስንወጣና ስንቀየር
  • 23:15 - 23:19
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ያነበብናቸውን
    እነዚያኑ ነገሮች በድጋሜ እናያለን፡፡
  • 23:19 - 23:24
    በዚያን ጊዜ በጣም ብዙ ነገሮች
    በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ተቀይረዋል፡፡
  • 23:26 - 23:30
    ከዛ በኋላ ጨለማው ጊዜያት ነበሩ፡፡
  • 23:30 - 23:34
    ምንም ያልሆነባቸው ብዙ ዓመታት፡፡
    በእርግጥ በተለያዩ ቦታዎች የክርስትና
  • 23:34 - 23:36
    መነቃቃቶች ሁል ጊዜ ነበሩ፡፡
  • 23:36 - 23:42
    ነገር ግን በትልቅ ቤተክርስቲያን የካቶሊክን ቤተክርስቲያን
    አገኘን ነገሮችም ሞተው ጠፉ፡፡
  • 23:42 - 23:48
    በዚያን ጊዜ ብዙ ነገሮች ተቀየሩ፡፡
    ከዚያ በ1500 ዓ.ም ማርቲን ሉተር የሚባል
  • 23:48 - 23:59
    አንድ ሰው በጀርመን ነበረ፡፡ እርሱ በኦክቶበር 31 1517 ዓ.ም
    ከ95 ጥናታዊ ጽሑፉ ጋር መጣ፡፡
  • 23:59 - 24:07
    ዘጠና አምስት ጽሑፎቹን በቤተክርስቲያኗ በር ላይ
    አኖራቸው (ለጠፋቸው)፣
  • 24:07 - 24:11
    ተሐድሶ ብለን የምንጠራውን ጅማሬም አየን
    -- የሉተራን ቤተ ክርስቲያንን አገኘን፡፡
  • 24:11 - 24:18
    ተሐድሶው በማርቲን ሉተር እስከተጀመረበት እስከ 1517
    ድረስ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ነበረን፡፡
  • 24:18 - 24:22
    እዚህ አለኝ: “ተሐድሶው፡፡”
  • 24:22 - 24:29
    በእውነቱ ላይ ነበር የተገነባው: በእምነት መጽደቅ
  • 24:29 - 24:34
    ስለዚህ ማርቲን ሉተር በእምነት መጽደቅ ከሚል ጋር መጣ፣
    የካቶሊክ ቤተክርስቲያን
  • 24:34 - 24:43
    ያጣችው ነገር፡፡ አሁን የምታዩት ማርቲን ሉተር ያደረገውና
    እግዚአብሔር እርሱን ጠርቶት
  • 24:43 - 24:49
    እንዲሠራ ያደረገው ነገር አስደናቂ ነበር፡፡
    የተደረገውን ተሐድሶ ብሎ መጥራት
  • 24:49 - 24:52
    በሆነ መልኩ ጥሩ ቃል ነው፡፡
  • 24:52 - 25:00
    ነገር ግን እርሱ በዚያን ጊዜ የካቶሊክ ቤተክርስተያንን ወደ
    ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በመመለስ አላደሳትም፡፡
  • 25:00 - 25:06
    ዛሬ በሉተራን ቤተክርስቲያን ውስጥ ብዙ ነገሮች
    የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ይመስላሉ፡፡
  • 25:06 - 25:10
    አሠራሩ ባጠቃላይ አሁንም የእሁድ ስብሰባዎች (ጉባኤ) ነው፣
    ሁሉንም ነገር የሚሠራው አሁንም ካህን ነው፣
  • 25:10 - 25:18
    አሁንም አንድ ትልቅ ቤተክርስቲያን ነው፣
    አሁንም ቁርባር ነው፣
  • 25:18 - 25:21
    አሁንም ጥቂት ዳቦና ወይን ነው፡፡
  • 25:21 - 25:25
    በሐዋርያት መጽሐፍ ውስጥ በአንድ ላይ
    ሆነው የሚመገቡትና
  • 25:25 - 25:28
    በምግብ የሚጠግቡበት እንደ ግብዣ ነበር፡፡
  • 25:28 - 25:32
    ያ ግን ተቀየረና በካቶሊክ ቤተክርስቲያን
    በኩል ሃይማኖታዊ ሆነ
  • 25:32 - 25:35
    በሉተራን ቤተክርስቲያንም ተመሳሳይ ነው
    ማለት ይቻላል፡፡
  • 25:36 - 25:42
    ማርቲን ሉተር በእምነት መጽደቅ ከሚል ጋር መጣ፡፡
    አዎ፣ ትክክል፡፡ ነገር ግን እርሱ
  • 25:42 - 25:47
    ሁሉንም አሠራር ወደ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
    መልሶ አላደሰውም፡፡
  • 25:47 - 25:51
    ቤተክርስቲያንን መልሶ ወደ ሐዋርያት ሥራ
    መጽሐፍ አልቀየራትም፡፡
  • 25:52 - 26:00
    አንድ ተጨማሪ ነገር፣ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን
    ብንመለከት፣ በዚህ ውስጥ በኋላ ላይ እሄድበታለሁ፣
  • 26:00 - 26:05
    እኛ ሁላችን ካህናት የሆንንበትንና እያንዳንዱ ሰው ማጥመቅ
    የሚችልበትን፣ እያንዳንዱ ሰው ቁርባን (የጌታን እራት)
  • 26:05 - 26:09
    መውሰድ የሚችልበትን፣ እያንዳንዱ ሰው የዚህ ሁሉ አካል
    መሆን የሚችልበትን ክህነት ኢየሱስ ይዞ መጣ፡፡
  • 26:09 - 26:13
    ምክንያቱም እኛ ሁላችን አንድ ሊቀ ካህናት
    ኢየሱስ ክርስቶስ ያለን ካህናቶች ነን፡፡
  • 26:14 - 26:18
    ያ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጊዜ ተቀየረ
    እናም
  • 26:18 - 26:23
    ጳጳሱን፣ ካህኑን፣ ሴትና ወንድ መነኮሳትን ያገኘንበትን
    አሠራር አገኘን፤ አንድ አጠቃላይ አሠራር አገኘን
  • 26:23 - 26:27
    ከዛም አጠቃላዩን አሠራር (system) አገኘን፡፡
    ከዛም ቁጭ ያሉ ሰዎችን (the lay people)፡፡
  • 26:27 - 26:31
    ይህም ኢየሱስ የሚጠላው ነገር ነው
    ምክንያቱም እኛ ሁላችንም አገልጋዮች ነን፡፡
  • 26:31 - 26:35
    በዚያ ውስጥም በቀጣዩ ትምህርት ውስጥ
    እሄድበታለሁ፡፡
  • 26:35 - 26:39
    ነገር ግን ተቀየረ
    ከዛም ተሐድሶውን አገኘን፡፡
  • 26:39 - 26:43
    በሉተራን ቸርች ውስጥ
    ሉተር ምን አደረገ?
  • 26:43 - 26:46
    ጳጳሱን አስወገደው፡፡
  • 26:46 - 26:48
    ስለዚህ አሁን ጳጳስ የለንም፡፡
  • 26:48 - 26:53
    ነገር ግን መልሶ
    ወደ ሁሉም አማኞች ክህነት
  • 26:53 - 26:58
    ያም በኤፌሶን 4፡11 እንደነበረው እናንተም ወደምታነቡለት
    ወደ አምስቱ አገልግሎቶች አልቀየረውም፡፡
  • 26:58 - 27:02
    ሰዎች ቅዱሳንን እያነፁ(ማነፅ) ወደነበረበት፡፡
    እርሱ ያን መልሶ አልቀየረውም፡፡
  • 27:02 - 27:07
    አልቀየረውም፣ እርሱ ጳጳሱን ብቻ አስወገደው አሁንም
    ካህኑ (ካህን) ነበረው እናም አሁን ሽማግሌዎችና
  • 27:07 - 27:10
    ሌሎች ነገሮች ነበሩት፡፡
  • 27:10 - 27:16
    ስለዚህ ያያችሁት አንድ ተሐድሶ ነበር ነገር ግን
    ተሐድሶው አልተፈጸመም(አልሰመረም)፡፡
  • 27:16 - 27:17
    ተሐድሶው
    ጅማሮ ብቻ ነበር፡፡
  • 27:18 - 27:24
    ምክንያቱም ልክ እንደ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን አንድ
    ትልቅ አሠራር (system) እየሆነ ስለመጣ፡፡
  • 27:25 - 27:30
    ስለዚህ እግዚአብሔር የሆነ ተጨማሪ ነገር መላክ
    ነበረበት፡፡ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያንን
  • 27:30 - 27:34
    ወደ መጀመሪያው መልሶ መውሰድ ፈልጓል
    ስለዚህ ቀጣዩን መነቃቃት ላከ፡፡
  • 27:34 - 27:42
    ያ በእንግሊዝ ውስጥ በ1600 መጀመሪያ ላይ በመጥምቃውያን
    (Baptist) መነቃቃት ሲጀምር አይተናል፡፡
  • 27:42 - 27:49
    በአማኞች ጥምቀት በማመናቸው የተነሣ ብዙ
    ሰዎች መከራ አግኝተዋል፡፡
  • 27:50 - 27:54
    እነርሱም በካቶሊክ ቤተክርስቲያንና
    በሉተራን ቤተክርስቲያን
  • 27:54 - 27:57
    እንዲሁም በካልቪኒስቲክ ቤተክርስቲያን
    መከራ ደርሶባቸዋል፡፡
  • 27:57 - 28:03
    እነርሱ ተሠቃዩ ስለዚህም በ1609
    ወደ ሆላንድ ሸሹ፡፡
  • 28:03 - 28:09
    የመጀመሪያውን የመጥምቃውያን ቤተክርስቲያን በሆላንድ
    አገኙ/አመጡ (አሁንም ድረስ ያ ቤተክርስቲያን አለን)፡፡
  • 28:09 - 28:14
    መጽሐፍ ቅዱሳዊ የአማኞች ጥምቀት አገኘን፡፡
  • 28:14 - 28:17
    ያገኘነው ይህን ነው፡፡
    እዚህ እናስቀምጠዋለን፡፡
  • 28:18 - 28:22
    በድጋሜም ስለ ጥምቀት ስታወሩ
    አንድ ዓይነት ነገር ታያላችሁ፡፡
  • 28:22 - 28:28
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ፣
    ሁሉም በዚያኑ ቀን በራሳቸው እምነት ተጠመቁ፡፡
  • 28:28 - 28:32
    ጥምቀትም፣ በግሪኩ ብትመለከቱ፣
    ከውኃ በታች [መሆን ነበረ]፡፡
  • 28:32 - 28:37
    ከውኃ በታች እንደመቀበር ነበር ያም
    የእውነት በጣም ጠቃሚ ነበረ፡፡
  • 28:37 - 28:41
    ጥምቀት በጣም ጠቃሚ ከመሆኑ የተነሣ
    ሳይጠመቅ ወደ እምነት የመጣ ማንንም
  • 28:41 - 28:47
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ አታገኙም፡፡
    ጥምቀት በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ በጣም ግልፅ ነው፡፡
  • 28:47 - 28:52
    ነገር ግን፣ አሁንም በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጊዜ
    በድጋሜ ተቀየረ ምክንያቱም
  • 28:52 - 28:55
    [በጊዜው] ብሄራዊ ሃይማኖት እየሆነ ስለመጣ፡፡ እና
    በአገሪቷ ግዛት ውስጥ ለነበረ ለሁሉም ሰው ስለነበረ፡፡
  • 28:55 - 29:00
    [በጊዜው] ከእንግዲህ በኋላ ስለ እምነት አልነበረም፡፡
    እያንዳንዱን ሰው፣ እያንዳንዱን ሕፃን አጠመቁ፡፡
  • 29:00 - 29:03
    ምክንያቱም በዚያን ጊዜ ምንም ምርጫ
    አልነበራቸውም፡፡
  • 29:04 - 29:09
    በዚያን ጊዜ የሕፃናት ጥምቀት
    ሲመጣ (እንደመጣ) እናያለን፡፡
  • 29:09 - 29:14
    ተሐድሶውን አግኝተናል፣ ነገር ግን
    የሉተራን ቤተክርስቲያንና ማርቲን ሉተር
  • 29:14 - 29:19
    ጥምቀትን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ
    እንምናነበው ቀየሩ ወይስ አደሱ?
  • 29:19 - 29:27
    አላደረጉትም፡፡ ምክንያቱም እሱ በዚህ ጥምቀት፣
    በሕፃናት ጥምቀት ቀጠለ፡፡
  • 29:28 - 29:31
    ስለዚህ ተሐድሶው እንዳልተፈጸመ
    በድጋሜ እናያለን፡፡
  • 29:31 - 29:34
    ሙሉ በሙሉ ስህተት በሆነ ነገር ላይ ነበር
    አሁንም ሲገነባ የነበረው፡፡
  • 29:34 - 29:40
    ስለዚህ የጥምቀት መነቃቃት አገኘን ከመነቃቃቱም
    መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነ ጥምቀት አገኘን፡፡
  • 29:41 - 29:43
    ነገር ግን እዛ አላቆመም፡፡
  • 29:44 - 29:50
    ከዛ በኋላ ነገሮች በመልካም መንገድ ጀመሩ፣ እነርሱ
    ሁልጊዜ ከቤተክርስቲያን ውጪ ይጀምራሉ፣
  • 29:50 - 29:55
    እንደ አንድ መነቃቃት እንቅስቃሴ፣ ሁልጊዜም
    የሆነ አስደናቂ ነገር በዚያ ነበረ፡፡
  • 29:55 - 29:58
    በዚያ መነቃቃት ነበረ፣ በዚያ እምነት ነበረ፣
    በዚያ እሳት ነበረ፡፡
  • 29:58 - 30:02
    ነገር ግን ባልታወቀ ምክንያት ሞተና
    አንድ አሠራር (a system) ሆነ፡፡
  • 30:02 - 30:05
    ዛሬ የሉተራን ቤተክርስቲያን በጣም
    የማርቲን ሉተር መልኩ አይደለም፡፡
  • 30:05 - 30:09
    ማርቲን ሉተር ከሉተራን ቤተክርስቲያን [ጋር ሲነፃፀር]
    እጅግ በጣም አክራሪ ነበር፡፡
  • 30:09 - 30:13
    የመጥምቃውያን ቤተክርስቲያንም ደግሞ ሲጀመር
    ከነበረው አንፃር [አሁን] አጥማቂ አይደለም፡፡
  • 30:13 - 30:20
    በእያንዳንዱ መነቃቃት ጊዜ ሁሉም ነገር
    በአስገራሚ መልክ እንደሚጀመር ልታዩ ነው፡፡
  • 30:20 - 30:24
    ከቤተክርስቲያን ውጭ ነጻነት ነበረ፣ ሕይወት ነበረ፡፡
    ወይ ቤተክርስቲያን ውስጥ ቢጀመር
  • 30:24 - 30:30
    ሳጥኑ እግዚአብሔር እያደረገ ያለውን ማቆየት
    ስለማይችል መፈንዳት ይኖርበታል፡፡
  • 30:30 - 30:37
    ሁል ጊዜ አዲስ ሃይማኖት ሲሆን፣ ሁል ጊዜ
    አንድ አዲስ የእምነት ማህበረሰብ፣
  • 30:37 - 30:42
    የእምነት ኔትዎርክ ወይም ድርጅት ወይም
    ምንም ብላችሁ ጥሩት ይሆናል፡፡
  • 30:43 - 30:47
    ከዚያ ይሞታል እናንተም ያንኑ
    ለሜተዲስቶች ማለት ትችላላችሁ፡፡
  • 30:48 - 30:53
    ጆን እና ቻርልስ ዌስሊ፣ ከ
    በእምነት መቀደስ ጋር መጡ፣ ይህም
  • 30:53 - 31:00
    ማርቲን ሉተር ያልተረዳው ነገር ነበር፣ ምክንያቱም
    ማርቲን ሉተር እኛ ከኃጢአት በታች
  • 31:00 - 31:07
    ነን እኛም ይህን አስመልክቶ ምንም ማድረግ አንችልም ብሎ
    ያምን ነበር፡፡ ቻርልስና ወንድሙ ጆን ዌስሊ ግን
  • 31:07 - 31:13
    እግዚአብሔር ቅዱሳን እንድንሆን እንደጠራንና ኢየሱስም
    ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ብቻ እንዳልመጣ አዩ፡፡
  • 31:13 - 31:16
    ነገር ግን ኢየሱስ መጥቶ የነበረበት ሌላው አላማ ደግሞ
    ነጻ ሊያወጣንና ኃጢአትን ሊወስድ ነው፡፡
  • 31:16 - 31:21
    እነርሱ የተረዱት አንድ ጠቃሚ እውነት ነበረ፡፡
  • 31:21 - 31:27
    ያም እውነት፡- እግዚአብሔር ቅዱስ እንደሆነ እኛም ቅዱስ
    መሆን እንደሚጠበቅብን፣ ስለዚህ ያ በኋላ ላይ እዚህ መጣ፡፡
  • 31:28 - 31:34
    በጣም አስደሳችና አጓጊ የሆነ ነገር
    አሁን ላሳያችሁ እፈልጋለሁ፡፡
  • 31:35 - 31:41
    ላለፉት ብዙ መቶ ዓመታት
    በዐይኖቻችን ፊት ለፊት ኢየሱስ
  • 31:41 - 31:46
    ወይም እግዚአብሔር የእርሱን ቤተክርስቲያን
    እያስመለሰ እንደሆነ ማየት ትችላላችሁ፡፡
  • 31:46 - 31:51
    በዚያ ጊዜ የጠፉትን ብዙ እውነቶች
  • 31:51 - 31:54
    የእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ወደምናነበው
    እርሱ መልሶ እያስመለሳቸው ነው፡፡
  • 31:55 - 32:01
    ወደ ዕብራውያን ምዕራፍ ስድስት ብትሄድ ለኛ እንዳማኞች
    (እንደአማኝነታችን) መሠረቱ ምን እንደሆነ
  • 32:01 - 32:11
    ታነባለህ፡፡ መሠረቱ ከክፉ አድራጎቶች
    (ከሞተ ሥራ) ንስሐ መግባት፣
  • 32:11 - 32:18
    በእግዚአብሔር ማመን እና ጥምቀት፣
    እነዚያ ሦስት ነገሮች መሠረቱ ናቸው፡፡
  • 32:18 - 32:25
    ንስሐ መግባት፣ በእግዚአብሔር ማመን እና ጥምቀት
    በዕብራውያን ስድስት ላይ የምታነበው(ቢው) ነው፡፡
  • 32:26 - 32:31
    እነዚህን ሦስቱን (ንስሐ መግባት፣ እምነት
    እና ጥምቀት) ብቻ እንኳ ብትወስድ፡፡
  • 32:31 - 32:33
    ስለነዚህ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
    ውስጥ የምናነበው ነው፡፡
  • 32:33 - 32:39
    የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ያጣችው የሆነ ነገር፣ ነገር ግን
    እግዚአብሔር በድጋሜ እንደአዲስ የጀመረው ነገር፡፡
  • 32:39 - 32:45
    መጀመሪያ እምነት መጣ፡፡ እኛ የጸደቅነው በእምነት ነው
    እንጂ በምፅዋት (ምፅዋት በመስጠት) አይደለም፡፡
  • 32:45 - 32:51
    የጸደቅነው ቤተክርስቲያን በመምጣት እና ትክክለኛውን
    ነገር በማድረግ አይደለም፣
  • 32:51 - 32:58
    የጸደቅነው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ነው፡፡
    ከዛ በውኃ መጠመቅ እና ከዚያ ቅድስናና ንስሐ፡፡
  • 32:58 - 33:05
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ተጀምረው ያየናቸው
    ነገሮች በዚያን ጊዜ [በካቶሊክ ቸርች ጊዜ]
  • 33:05 - 33:11
    ተቀይረው ታያለህ(ሽ)፡፡ እግዚአብሔር ግን በድጋሜ
    እንደአዲስ ጀመረው ይህን ማድረጉንም ቀጠለው፡፡
  • 33:11 - 33:16
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ የሚታነቡት
    ቀጣዩ ነገር የዘላለም ሕይወት ነው፡፡
  • 33:16 - 33:20
    ከዚያም እጆችን ከመጫን ጋር ስለተያያዘው፣
    መንፈስ ቅዱስን ስለመቀበል ነው፡፡
  • 33:20 - 33:27
    ያም እግዚአብሔር የላከው ቀጣዩ ነገር ነበር፡፡
    ቀጣዩ ነገር: የአድቬንቲስት ቤተክርስቲያን፣
  • 33:27 - 33:31
    የክርስቶስ ሁለተኛ [ጊዜ ተመልሶ]
    የመምጣት ተስፋ፡፡
  • 33:31 - 33:36
    የክርስቶስ ሁለተኛ [ጊዜ ተመልሶ] የመምጣት ተስፋ፣
    የአድቬንቲስት ቤተክርስቲያን፡፡ እዚህ ጋር እናስቀምጠዋለን፡፡
  • 33:37 - 33:42
    ከዚያ በኋላም ቀጣዩን አገኘን፡፡
    እዚህ ጋር ጽፌአለሁ:
  • 33:42 - 33:47
    ፊኔይ እና ሙዲ:
    በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ
  • 33:47 - 33:53
    ያ ቅዱሳንን ለማነፅ ነበር፡፡
    ስጦታዎቹ ሳይሆኑ፣ ራሱ መንፈስ ቅዱስ፡፡
  • 33:53 - 33:56
    ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ፣
    ምሥክር ለመሆን [የሚያስፈልገው] ኃይል፡፡
  • 33:56 - 34:00
    እነርሱ ይዘውት የመጡት ነገር እና
    እግዚአብሔር ለማምጣት እነርሱንና
  • 34:00 - 34:02
    በዚያን ጊዜ የነበሩ ሌሎች ሰዎችን
    ተጠቀመባቸው፡፡
  • 34:02 - 34:08
    ያ ሲመጣም፣ የሁሉንም ነገር
    የታደሰ ጎን በድጋሜ አየን፡፡
  • 34:08 - 34:12
    መንፈስ ቅዱስ መጣ እናም
    ኃይሉና ሕይወት መሆን ጀመረ፡፡
  • 34:12 - 34:19
    ነገር ግን አሁንም በዚህ ጊዜ የቤተክርስቲያንን
    ታሪክ ብትመለከቱ በእምነት መጽደቅን፣
  • 34:19 - 34:26
    በእምነት መቀደስን እናያለን፣ አዎን (yes)!
    መጽሐፍ ቅዱሳዊ የአማኞች ጥምቀት፣ አዎን!
  • 34:26 - 34:28
    የኢየሱስ መምጣት ተስፋ፣ አዎን!
  • 34:29 - 34:33
    በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅም፣ አዎን!
    ኃይሉ፣ አዎን!
  • 34:33 - 34:38
    ነገር ግን በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
    ውስጥ የምናነባቸው ስጦታዎች:
  • 34:38 - 34:42
    በልሳኖች መናገር፣ ትንቢት መናገር፣
    አጋንንትን ማስወጣት፣ ህሙማንን መፈወስ
  • 34:42 - 34:48
    በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ የጠፉት ነገሮች ነበሩ
    እነዚያ ቤተክርስቲያኖች አሁንም እየገነቡ አይደለም፡፡
  • 34:48 - 34:52
    ለምን? ምክንያቱም ይህ የእነርሱ መሠረት
    ስላይደለ፡፡ ግልፁን ለመናገር፡፡
  • 34:52 - 34:56
    የእነርሱ መሠረት ባህል ነው እንጂ
    መጽሐፍ ቅዱስ አይደለም፡፡
  • 34:56 - 35:01
    እንዲህ ዓይነት ነገር መናገር
    እንደሚያስቆጣ አውቃለሁ፡፡
  • 35:01 - 35:05
    ነገር ግን ይህን በግልፅ ማየት ትችላላችሁ:
    አሁንም ነን፣ እኔም የዛ አካል ነበርኩ፡፡
  • 35:05 - 35:08
    እያንዳንዳችን የዚህ ታሪክ አካል ነን፡፡
  • 35:08 - 35:11
    በተሳሳተ (ትክክል ባልሆነ) መሠረት ላይ
    እየገነባን ነበርን፡፡
  • 35:11 - 35:15
    ዛሬ ሕይወቱን የማታዩባቸው እጅግ በጣም
    ብዙ ቤተክርስቲያኖች አሉን፣
  • 35:15 - 35:19
    ስጦታዎቹን አታዩም
    ትክክለኛው ቲዖሎጂም የላችሁም፡፡
  • 35:19 - 35:26
    ስለዚህ እግዚአብሔር አዲስ ነገር ላከ:
    ፔንቴኮስት፣ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች፡፡
  • 35:26 - 35:32
    አዙሳ ጎዳና፣ በ1906 ዓ.ም ሎስ አንጀለስ፣
    ደብሊው. ጄ. ሴይሞውር፡፡
  • 35:32 - 35:34
    በአንድ ላይ ሆነው የሚጸልዩ
    አንድ የሰዎች ቡድን ነበር፡፡
  • 35:34 - 35:40
    መንፈስ ቅዱስ መጣና በእነርሱ ላይ ወረደ
    ስጦታዎቹም ለቤተክርስቲያን
  • 35:40 - 35:42
    አንድ ተጨማሪ ጊዜ ታድሰው ነበር፡፡
  • 35:45 - 35:52
    በዚያው ጊዜ በዌልስ ከኢ. ሮበርትስ ጋር
    ሌላ መነቃቃት ነበረን፡፡
  • 35:52 - 35:58
    በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ 100,000 ሰዎች
    የዳኑበት በጣም አስደናቂ መነቃቃት ነበረ፡፡
  • 35:58 - 36:00
    ሰዎችም በእርግጥ
    የእውነት ንስሐ ገብተዋል፡፡
  • 36:00 - 36:05
    አክራሪ ወይም መሠረታዊ ነበር እነርሱም ፀባይ ማረሚያዎችን
    (እስር ቤቶችን) መጠጥ ቤቶችንም፣ እንዲሁም ሁሉንም ነገር ዘጉ፡፡
  • 36:05 - 36:08
    ሰዎች መስረቅና መሳደብ ማቆም ጀመሩ፡፡
  • 36:08 - 36:13
    በዌልስ መነቃቃት ጊዜ
    በጣም ብዙ ነገሮች ሆኑ፡፡
  • 36:13 - 36:20
    ከዚያ መነቃቃት ውስጥም ጠፍቶ
    የነበረ አንድ እውነት መጣ፡፡
  • 36:20 - 36:23
    ያም አምስቱ አገልግሎት ነበር፡፡
  • 36:23 - 36:30
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ እንደምናነበው፣
    ነገር ግን እንደ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በፍፁም አልሆነም፡፡
  • 36:30 - 36:35
    ምክንያቱም፣ አሁንም በእነዚያ ቤተክርስቲያን
    ውስጥ አለን፣ መላው ሳጥን አሁንም አለን፡፡
  • 36:35 - 36:40
    ስለ ካህናት እንደምናነበው፡፡
    ስለዚህ አምስቶቹ አገልግሎት
  • 36:40 - 36:43
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ እንደምናነበው
    ትክክለኛውን ቦታ አላገኙም፡፡
  • 36:44 - 36:49
    ወደዛ በኋላ ላይ ተመልሼ እመጣሁ፡፡ ከዚያ
    ውስጥም ሐዋርያዊ ቤተክርስቲያንን አገኘን፡፡
  • 36:49 - 36:53
    ዴንማርክ ውስጥ አንድ እንቅስቃሴ አለን፣
    የሐዋርያዊ ቤተክርስቲያን ተብሎ የሚጠራ ኔትዎርክ፡፡
  • 36:53 - 36:57
    መሠረታቸውን በዌልስ
    ሪቫይቫል ውስጥ ያደረጉ፡፡
  • 36:58 - 37:03
    ይህ የሆነ የቤተክርስቲያን ታሪክ ነው፣
    እኔ በዚያ ውስጥ ብቻ እየወሰድኳችሁ ነው፡፡
  • 37:03 - 37:07
    እኛም ከዚህ ከቤተክርስቲያን ታሪክ
    ውስጥ በጣም ብዙ መማር እንችላለን፡፡
  • 37:08 - 37:14
    ዛሬ እያደረግን ያለናቸውን ነገሮች ለምን
    እያደረግናቸው እንደሆነ መማር እንችላለን፡፡
  • 37:14 - 37:23
    ምክንያቱም አጠቃላዩን መነሻ (መቼት)፣ ህይወትን
    ከቦ ያለውን ሳጥን መመልከት ከጀመርንና
  • 37:23 - 37:27
    የቤተክርስቲያንን ሕንጻ ስንመለከት፡፡
  • 37:27 - 37:32
    እነርሱ (በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ) እኛ አሁን
    የቤተክርስቲያን ሕንጻ ባለን መልኩ የላቸውም ነበር፡፡
  • 37:32 - 37:35
    እኛ አሁን ባለን መልኩ የእሁድ
    ስብሰባ እነርሱ የላቸውም ነበር፡፡
  • 37:35 - 37:40
    እኛ ባለን መልኩ እነርሱ የእሁድ አምልኮ
    ቅደምተከተል የላቸውም ነበር፡፡
  • 37:40 - 37:43
    ሁሉም ነገር አንድ አይነት የሚመስልበት፣
    ልክ በአንድ ሳጥን ውስጥ እንደመቀመጥ፡፡
  • 37:44 - 37:46
    እነርሱ ያ የላቸውም ነበር፡፡
  • 37:47 - 37:50
    በጣም ብዙ ነገሮች በካቶሊክ
    ቤተክርስቲያን በኩል ተቀይረዋል፡፡
  • 37:50 - 37:54
    ሕንጻውን አገኘን፣ ካህናቱን አገኘን፣ ዛሬ
    ካለን ከእሁድ አምልኮ ቅደምተከተል ጋር
  • 37:54 - 37:59
    የእሁድ ስብሰባዎችን አገኘን፡፡
  • 38:00 - 38:08
    ያ ተቀየረ፡፡ የካቶሊክ ቤተክርስቲያንና የሉተራን
    ቤተክርስቲያንም አንድ አይነት ይመስላሉ፡፡
  • 38:08 - 38:12
    እያንዳንዱም ሌላ ቤተክርስቲያን
    የሉተራንን ቤተክርስቲያን ይመስላል፡፡
  • 38:13 - 38:16
    የእሁድ ስብሰባ፡፡ በእርግጥ፣
    አንዳንዶች ቅዳሜ ነው ያላቸው፡፡
  • 38:16 - 38:21
    የእሁድ ስብሰባ፣ የእሁድ ስብሰባ፣
    የእሁድ ስብሰባ፣ የቤተክርስቲያን ሕንፃ፡፡
  • 38:21 - 38:23
    ሁሉም ነገር በሆነ መልኩ አንድ አይነት ይመስላል!
  • 38:23 - 38:30
    ዛሬ በዓለም ውስጥ ብትጓዙ፣ ሁሉም ቤተክርስቲያን
    ማለት ይቻላል አንድ አይነት ይመስላል፡፡
  • 38:30 - 38:34
    ሁል ጊዜ ቃሉን ይዞ የሚቆም
    አንድ ፓስተር አለን:
  • 38:34 - 38:41
    “በእኛ ቤተክርስቲያን ውስጥ ቃሉ ላይ ነው
    እየገነባን ያለነው፣ ቃሉንም ብቻ፡፡”
  • 38:41 - 38:44
    እነርሱ ያን እያሉ ነው ነገር ግን እየገነቡበት
    ያለው ጠቅላላው መሠረት፣
  • 38:44 - 38:47
    ወደ ቅንብሩ (መቼቱ) ስንመጣ፣
    ወደ ሕንጻው ሲመጡ፣
  • 38:47 - 38:52
    ወደ [ሥልጣን] ተዋረዱ ሲመጡ፣
    ወደ ቤተክርስቲያን ስብሰባ ሲመጣ፡፡
  • 38:52 - 38:57
    መጽሐፍ ቅዱስ [ቅዱሳዊ] አይደለም፣ ነገር ግን በ300 ዓ.ም
    እና ከዛ በኋላ የሆነችው የካቶሊክ ቤተክርስቲያናዊ ነው፡፡
  • 38:57 - 39:03
    በዚያም ምክንያት፣ በሆነ መልኩ ሕይወት
    ከሰዎች ውስጥ እየወጣ ነው፡፡
  • 39:03 - 39:06
    ሁላችንም እግዚአብሔርን
    ለማገልገል ስለተጠራን!
  • 39:06 - 39:09
    በቀጣዩ ትምህርት
    ስለዛ ላወራ ነው፡፡
  • 39:09 - 39:11
    ሁላችንም እግዚአብሔርን ለማገልገል
    ስለተጠራን፡፡
  • 39:11 - 39:16
    አንተም ቤተክርስቲያን መጥተህ ብቻ ብታዳምጥ
    ከዛም አንዳች ነገር ባታደርግ፣
  • 39:16 - 39:20
    ቀስ በቀስ እየሞትክ ነው
    ይህንም ነው ዛሬ [ላይ] እያየን ያለነው፡፡
  • 39:20 - 39:26
    ምክንያቱም የዚያ ቤተክርስቲያን ቅንብር ደቀ
    መዛሙርት ለማድረግ (ለማፍራት) አይችልም፡፡
  • 39:26 - 39:30
    የራሴን ህይወት ምስክርነት
    መናገር እፈልጋለሁም፡፡
  • 39:30 - 39:38
    የዳንኩት ከእነዚያ ሳጥኖች በአንዱ ውስጥ ነው፡፡
    ወደ አንድ ቤተክርስቲያን መጣሁና በዙሪያዬ ተመለከትኩ፡፡
  • 39:38 - 39:43
    እንዲህም ብዬ አሰብኩ: “ይህን ነው የማየው፣ ይህ
    ኖርማሉ (መደበኛው) የክርስቲያን ሕይወት ነው፡፡”
  • 39:43 - 39:49
    እኔም፣ እንደ ብዙዎች ሌሎች፣ እግዚአብሔርን ለማገልገል
    መሻትና ጥልቅ መሻት ነበረኝ እንዲህም አልሁ:
  • 39:49 - 39:53
    “እሺ፣ እግዚአብሔርን እንዴት ነው ማገልገል የምችለው?”
    እግዚአብሔርን እንዴት ማገልገል እችላለሁ ብዬ
  • 39:53 - 39:56
    እያሰብኩ ዙሪያውን እየተመለከትኩ ነበር፡፡ “እሺ፣ መዘመር
    አልችልም፣ የአምልኮ አካል መሆን አልችልም፡፡
  • 39:56 - 40:03
    ምክንያቱም በህይወቴ ውስጥ ምንም ድምፅ (ቅላፄ) የለኝም፡፡”
    “እሺ፣ መስበክ እፈልጋለሁ ነገር ግን ያን ማድረግ አልችልም
  • 40:03 - 40:06
    ምክንያቱም ይህ በሌላ ሰው ተወስዷል፡፡”
  • 40:06 - 40:11
    ስለዚህ አስተናጋጅ ሆንኩኝና በተግባራዊ
    ነገሮች ረዳሁኝ፡፡ ተስማምቼ ነበር፡፡
  • 40:11 - 40:17
    ነገር ግን ከሆኑ ዓመታት በኋላ አስታውሳለሁ፡፡ ለበለጠ [ነገር]
    ጥልቅ መሻት ነበረኝ፡፡ ለመስበክ ፈለግሁ፡፡
  • 40:17 - 40:22
    ምክንያቱም በድጋሜ እዚያ ቤተክርስቲያን ውስጥ ላደርገው
    የምችለው ብቸኛው ነገር ያ እንደሆነ አየሁ፡፡
  • 40:22 - 40:25
    ስለዚህ ለጓደኛዬ እንዲህ አልኩት: “እንዴት
    ነው ለመስበክ መምጣት የምችለው?”
  • 40:25 - 40:29
    እርሱም እዛ (መስበክ) ላይ መገንባት ትችላለህ፡፡
    የሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ጀምር፡፡
  • 40:29 - 40:31
    ከሆኑ ዓመታት በኋላ የወጣቶች
    መሪ ልትሆን ትችላለህ፡፡
  • 40:31 - 40:36
    የወጣቶች መሪ ሆነህ ከሆኑ ዓመታት በኋላ
    በየዓመቱ አንድ እሁድ ትሰብካለህ አለኝ፡፡
  • 40:36 - 40:41
    እርሱ ያን ነገረኝ፡፡ እጄን ተመለከትሁ እናም
    እንደዚህ አሠራር እያንዳንዱን ነገር ካደረግሁ፣
  • 40:41 - 40:48
    በየዓመቱ አንድ እሁድ ለመስበክ እድል
    ለማግኘት አምስት ዓመት ይፈጅብኛል፡፡
  • 40:48 - 40:53
    በሆነ መልኩ ዐይኖቼን ከፈተው፡፡ በድንገት ዙሪያዬን
    ተመለከትኩ በጣምም ደንግጬ ነበር!
  • 40:53 - 40:57
    ምክንያቱም በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ውስጥ
    የነበሩ፣ እግዚአብሔርን ያውቁ የነበሩ ብዙ ሰዎች እዚህ ነበሩ፡፡
  • 40:57 - 41:02
    ሕይወቱ ግን የት አለ? እነርሱ ይመጣሉ ብቻ
    ይቀመጣሉም አያገለግሉምም፡፡
  • 41:02 - 41:06
    ምንም እየሆነ አልነበረም!
    የሆነ የተሳሳተ ነገር እንደነበረ አየሁ፡፡
  • 41:06 - 41:10
    በዚያም ምክንያት እኔና ሚስቴ
    ሌሎች ሰዎች አንድ
  • 41:10 - 41:12
    ቤተክርስቲያን ሲገነቡ ለመርዳት
    ወደ ሌላ ከተማ ሄድን፡፡
  • 41:12 - 41:17
    በዚያን ጊዜ ወጣቶች ነበርን በእሳት ላይም
    ነበርን፡፡ በኛ ላይ ማንም አልነበረም፡፡
  • 41:17 - 41:20
    ስለዚህ ማድረግ የፈለግነውን ያንኑ
    ለማድረግ ነጻ ነበርን፡፡
  • 41:20 - 41:27
    አስታውሳለሁ: “አሁን ነጻ ነን፣ አዎን!”
    የመጀመሪያውን የእሁድ ስብሰባ ልናደርግ
  • 41:27 - 41:31
    እንደነበረ አስታውሳለሁ: “ምን እናድርግ?
    አንተ ልትሰብክ ነው፡፡
  • 41:31 - 41:35
    ኦህ፣ ጥሩ ሊሆን ነው! አንድን
    ስብሰባ ልመራ ነው፣ ዉ!”
  • 41:35 - 41:38
    “ግን ደግሞ መብዓም ልንወስድ ፈለግን፡፡”
  • 41:38 - 41:41
    “አዎ፣ ነገር ግን ዝም ብለን መብዓ መውሰድና
    ከዚያም መስበክ አንችልም፡፡”
  • 41:41 - 41:46
    “አይሆንም፣ እንኳን በደህና መጣችሁ ብልና
    አንዳንድ መዝሙሮችን ብዘምርስ፡፡
  • 41:46 - 41:49
    ከዚያም አንዳንድ መረጃ ሰጥተን
    ከዚያ መብዓ ብንሠበስብስ?
  • 41:49 - 41:54
    ከዚያም ተጨማሪ መዝሙሮች አሉን ከዚያም
    ብሰብክስ?” “አዎ! ያን እናድርግ!”
  • 41:54 - 42:01
    ወረቀቱን አይቼ ይህ የተለየ አለመሆኑን!
    እስካይ ድረስ በጣም ደስተኛ ነበርኩ
  • 42:01 - 42:05
    ይህ ጥለነው የመጣነው ያው ነው!
  • 42:07 - 42:15
    እኛም መረዳት ያለብን ይህን ነው፡፡ ትቼ የወጣሁት
    ደቀ መዛሙርት ማድረግ (ማፍራት) እፈልግ ስለነበረ ነው፡፡
  • 42:15 - 42:19
    ያን መቀየር ፈልጌ ነበር፡፡ ነገር ግን አሮጌውን
    ነገር መተው በራሱ አንድ ነገር ነበር፡፡
  • 42:19 - 42:22
    አሮጌውን ነገር ከኔ ውስጥ ማውጣት ደግሞ
    ሌላ ነገር ነው፡፡
  • 42:22 - 42:27
    እንደ ሙሴ፣ እስራኤላውያንን ከግብፅ ማውጣት
    ለእርሱ በጣም አስቸጋሪ አልነበረም፡፡
  • 42:27 - 42:31
    ነገር ግን ግብፅን ከእነርሱ ውስጥ ማውጣት አስቸጋሪ ነበረ፡፡
    እነርሱ ሁል ጊዜ ወደ ኋላ ይመለከቱ ነበር፡፡
  • 42:31 - 42:38
    እኔም፣ ዳንኩኝ እና ወደ ቤተክርስቲያን መጣሁ
    እናም ያን ትቼ ከወጣሁ ከአጭር ጊዜ በኋላ፣
  • 42:38 - 42:43
    የሆነ አዲስ ነገር መገንባት ፈለግሁ፡፡ ደቀ መዛሙርቶች
    ማድረግ (ማፍራት) ፈልጌ ነበር፡፡ ምን ሆነ?
  • 42:43 - 42:46
    አንዴ በድጋሜ ከአሮጌው ነገር ጋር ሆንኩ፡፡
  • 42:46 - 42:50
    እንኳን ደህና መጣችሁ፣ አንዳንድ መዝሙረች፣
    መረጃ፣ መብዓ፣ መዝሙሮች፣
  • 42:50 - 42:58
    ከዛ ትሰብካለህ ከዛም ቁርባን ከምንወስድበት
    የእሁድ ስብሰባ ጋር ሆንኩ (ended up with)፡፡
  • 42:58 - 43:02
    ይህም ትቼው ከመጣሁት ጋር
    አንድ አይነት ይመስል ነበር፡፡
  • 43:02 - 43:06
    በመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ውስጥ
    ከምናነበው እጅግ በጣም የራቀ ይመስላል፡፡
  • 43:06 - 43:10
    እነርሱ እንደዚያ ዓይነት ቅደም
    ተከተል የላቸውም ነበር፡፡
  • 43:10 - 43:15
    አሁን ግን ከብዙ ዓመታት በኋላ በዴንማርክ ውስጥ
    ያ ቅደም ተከተል አለኝ፡፡ ለምን?
  • 43:15 - 43:18
    ምክንያቱም ከቤተክርስቲያኔ የኋላ ታሪክ የተነሣ፣
    ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተነሣ፡፡
  • 43:18 - 43:26
    በሆነ መልኩ ቀጥሏል እኛም ሁላችን
    የእነዚያ ባህሎች አካል ነን፡፡ የኔም ታሪክ
  • 43:26 - 43:29
    ያን ቦታ ትተን ወደ ሌላ ቦታ ሄድን በድጋሜም
    ቤተክርስቲያን ተከላ ላይ ሠራን፡፡
  • 43:29 - 43:31
    በእያንዳንዱ ጊዜም አንድ ጥቂት
    ተጨማሪ ነገር ተማርሁ፡፡
  • 43:31 - 43:37
    በሆነ መልኩ ግን፣ ከዚያ ሳጥን ውስጥ ሰብሮ ለመውጣት፣
    ከባህሉ ውስጥ ሰብሮ ለመውጣት ቀላል አልነበረም፡፡
  • 43:37 - 43:42
    በስተመጨረሻ ግን እግዚአብሔር አንድ ሕልም
    ሰጠኝ እኔም ነጻነቱን ተለማመድሁ (experience)፡፡
  • 43:42 - 43:47
    ነጻነቱን ስለማመድ (ስቀምስ)፣
    በጣም ብዙ ነገረች ተቀየሩ፡፡
  • 43:47 - 43:54
    እኛም ወደ ሌላ ከተማ ተንቀሳቀስን (ሄድን)
    በዚያም የሆነው ነገር
  • 43:54 - 43:59
    እግዚአብሔር ወደ ምድረበዳ ወሰደን፡፡
    ቤታችንን አጣን፣ ገንዘባችንን አጣን፡፡
  • 43:59 - 44:03
    በዚያን ጊዜ ሚስቴ ታማ ነበር፣ በአልጋ ላይ
    ተኝታ ነበር እኔም መሞት ፈልጌ ነበር፡፡
  • 44:03 - 44:05
    ከአራት አመት በፊት ወይም
    እዚያ አካባቢ ነበር ይህ የሆነው፡፡
  • 44:05 - 44:10
    ለመሞት ዝግጁ ነበርኩ ምክንያቱም “እግዚአብሔር
    ሆይ የት ነው ያለኸው?” እያልኩ እየጠየኩ ነበር፡፡
  • 44:10 - 44:18
    በዚያ ጊዜ ሁሉን ነገር አጣን፡፡
    ሁሉን ነገር ስናጣ ግን ኢየሱስን አገኘን፡፡
  • 44:18 - 44:24
    እኔ የቤተክርስቲያን አባል ያልሆንኩበት
    2 ወይም 1 ½ ዓመት ጊዜ ነበረኝ፡፡
  • 44:24 - 44:27
    ስለዚህ ሁሉን ነገር ከውጪ ሆኜ እያየሁ ነበር፡፡
  • 44:27 - 44:30
    ሁሉን ነገር ከውጪ ሆኜ ሳይ፣
  • 44:30 - 44:33
    በድንገት ነገሮችን በአዲስ መልኩ ማየት ጀመርሁ፡፡
  • 44:33 - 44:38
    ልክ መነጽሮቼ ከዐይኖቼ ላይ እንደወለቁ ዓይነት
    እኔም ነገሮችን በአዲስ መልኩ አየሁ፡፡
  • 44:38 - 44:43
    ያ ለኔ አዲስ ህይወት ፈጠረልኝ፡፡
    እኔም አንድ ምስክርነት መናገር እችላለሁ፡፡
  • 44:43 - 44:47
    በዚያን ጊዜ ለአርባ ቀናት እየፆምኩ ነበር፡፡
  • 44:47 - 44:51
    አንድ ቀንም እግዚአብሔር ተናገረኝ እንዲህም
    አለ: “ቶርበን” እኔም: “ምን!” አልኩ፡፡
  • 44:51 - 44:56
    “ወደ ኔይስትቬድ ሂድ”፣ በሌላኛው
    የዴንማርክ ጫፍ ያለ ከተማ ነው፡፡
  • 44:56 - 45:02
    የተናገረኝ እግዚአብሔር እንደሆነ አውቄ ነበር እኔም
    እያለቀስኩ ወደ ቤት ሄድኩ፡፡ “ኦህ ወደ ኔይስትቬድ ልንሄድ ነው”
  • 45:02 - 45:05
    ያ ለኔ በጣም ጠንካራ ነበር ስለዚህ ወደ
    ኔይስትቬድ ሄድን፡፡
  • 45:05 - 45:10
    እዚያ ሄድኩና: “እግዚአብሔር፣ አሁን እዚህ ነኝ
    ምን እንዳደርግ ነው የምትፈልገው?” አልኩ፡፡
  • 45:10 - 45:14
    እግዚአብሔርን እየተጠባበቅሁና እየጸለይኩ
    በዚያው አካባቢ ተዘዋወርኩ፡፡
  • 45:14 - 45:18
    ከዚያም በእሁድ በዚያ አንድ ትንሽ የመጥምቃውያን
    ቤተክርስቲያን ነበረ እዚያም ተናገርሁ፡፡
  • 45:18 - 45:20
    እዚያ ፓስተር (እረኛ) የሆነ
    አንድ ጓደኛ አውቃለሁ፡፡
  • 45:20 - 45:23
    እዚያም አንድ ሰው ወደኔ መጣ እኔም ጸለይኩለት፡፡
  • 45:23 - 45:28
    ጉልበቱ ላይ አንድ ችግር ነበረበት ከአንድ ሳምንት
    በኋላም [በሆስፒታል] ሊታከም[ቀዶ ጥገና ሊደረግለት] ነበረ፡፡
  • 45:28 - 45:30
    ለእርሱ ጸለይኩለት እግዚአብሔርም ፈወሰው፡፡
  • 45:30 - 45:33
    ያለምንም ችግር ደረጃዎችን
    መውጣትና መውረድ ቻለ፡፡
  • 45:33 - 45:37
    ከስብሰባው በኋላ ወደኔ መጣ፡፡
    “ቶርበን፣ ላናግርህ ያስፈልገኛል፡፡
  • 45:37 - 45:40
    እግዚአብሔር መቼ ነው ወደ ኔይስትቬድ
    ስለመሄድ የተናገረህ?” አለ፡፡
  • 45:40 - 45:42
    እኔም ተመለከትኩት:
  • 45:42 - 45:48
    “የመጀመሪያው ከሰዓት በኋላ ሜዳው ላይ በ9ኝ
    ሰዓት እየጸለይኩ ሳለ፡፡ ለምን [ጠየቅኸኝ]? ”
  • 45:48 - 45:52
    እርሱም አለ: “ቶርበን ይህ አስገራሚ ነው፣
    ዌብሳይትህን ያገኘሁት ሰኞ ነበር፡፡
  • 45:52 - 45:56
    እኔም ደግሞ ሰኞ፣ ማክሰኞ እና ረቡዕ ወደ
    እግዚእብሔር እየጸለይኩ ነበር፡፡”
  • 45:56 - 46:01
    “እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔ እፈወስ ዘንድ እርሱ ለኔ
    መጸለይ እንዲችል ቶርበንን ወደ ኔይስትቬድ ላከው፡፡”
  • 46:01 - 46:05
    እኔም እንዲህ አልኩ: “ምን?”፡፡
    ያን ስሰማ እንዲህ ብዬ አሰብኩ:
  • 46:05 - 46:11
    “ዉ-ኦው! እዚህ በሌላኛው የዴንማርክ ጫፍ ሆኜ
    እየጸለይኩኝ፡፡ እግዚአብሔር ተናገረኝ:”
  • 46:11 - 46:17
    “እዚያ ሂድ እኔም ሄድኩ ምክንያቱም
    ይህ ሰው እየጸለየ ነበረ እርሱም ተፈወሰ፡፡”
  • 46:17 - 46:21
    ወደ ቤት እየሄድኩ ሳለ ለሚስቴ እንዲህ አልኳት:
  • 46:21 - 46:25
    “የምንፈልገው ይህን ነው! በመንፈስ ቅዱስ
    እየተመራን ያለንበትን ይህን ሕይወት፡፡”
  • 46:25 - 46:29
    አሁን እንደዚህ ዓይነት በመቶዎች የሚቆጠሩ
    ምስክርነቶች አለኝ፡፡
  • 46:29 - 46:35
    መንፈስ ቅዱስ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን እንዴት
    እየመራንና [በምክር] እያቀናጀን እንዳለ፡፡
  • 46:35 - 46:41
    ከእነዚያ የባህል ሳጥኖች ውስጥ ሰብሮ መውጣት
    ስጀምር፣ ወዲያውኑ ማን እንደነበርሁ አየሁ፡፡
  • 46:41 - 46:45
    ካህን ነበርሁ፣ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቼ ነበር፡፡
    እኔ የእግዚአብሔር መቅደስ ነበርኩ፡፡
  • 46:45 - 46:52
    እግዚአብሔር በዕለት ተዕለት ሕይወት ሊጠቀምብኝ ይችላል!
    ያም ወደ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ተመልሼ እንድመጣ ረዳኝ፡፡
  • 46:52 - 46:54
    አብሬው (አብሬያት) ስሠራና ሳሰለጥነው
    የነበረ እያንዳንዱ ሰው ከዚያን ጀምሮ
  • 46:54 - 46:58
    ይህን ትምህርት እየሰጠኋቸው እነርሱም
    ተመሳሳይ ልምምድ አግኝተዋል:
  • 46:58 - 47:01
    ከእነዚያ ባህሎችና የአዕምሮ-ቅንብሮች (mind-sets)
    ውስጥ ሰብረው ሲወጡ፣
  • 47:01 - 47:06
    በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የምናነብለትን
    ሕይወት ወዲያውኑ መለማመድ ጀመሩ፡፡
  • 47:06 - 47:11
    ይህ ነው ትምህርቴ፡፡ ብዙው አስተምህሮቴ
    ምድረበዳ ሄደን ነገሮችን በአዲስ መልኩ
  • 47:11 - 47:17
    ካየንበትና ከእነዚያ ባህሎች ሰብረን
    ከወጣንበት ከዚያ ጊዜ የመጣ ነው፡፡
  • 47:17 - 47:26
    ከመጀመሪያው ይህን ማለት እፈልጋለሁ: ቤተክርስቲያንን
    እወዳለሁ፣ ከቤተክርስቲያን ተቃራኒ አይደለሁምም፡፡
  • 47:26 - 47:32
    ነገር ግን አንድ ተሐድሶ ማየት እፈልጋለሁ፡፡
    እንደ ሉተርም፣ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን:
  • 47:32 - 47:37
    ሉተር የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ለማደስ ሲጀምር
  • 47:37 - 47:41
    ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት
    ከሰይጣን የተላክ ነበር አሉት፡፡
  • 47:41 - 47:44
    ማርቲን ሉተር ከቤተክርስቲያን በተቃራኒ
    እንዳልነበረ ዛሬ ግን አውቀናል፡፡
  • 47:44 - 47:48
    ሊያድሳት ብቻ ነበር የፈለገው፡፡
    እኔም ከቤተክርስቲያን በተቃራኒ አይደለሁም፣
  • 47:48 - 47:50
    ቤተክርስቲያንን ማደስ እፈልጋለሁ፡፡
  • 47:50 - 47:54
    ነገር ግን እኔ ስለቤተክርስቲያን ያለኝ ዕይታ
    ስለቤተክርስቲያን ካሉ ሌሎች ዕይታዎች በጣም የተለየ ነው፡፡
  • 47:54 - 47:59
    ዛሬ በብዙ ቤተክርስቲያኖች እየተናገርኩ ነው:
    በፔንቴኮስታል፣ በባፕቲስት (መጥምቃውያን) እና
  • 47:59 - 48:06
    በተለያዩ ዓይነቶች ቅንብሮች(አሠራሮች) ውስጥ፡፡ እዚያ
    መናገር እችላለሁ በሆነ መልኩም ደግሞ [ቅንብሩን] አከብራለሁ፡፡
  • 48:06 - 48:11
    ነገር ግን ይህን አምናለሁ ደቀ መዛሙርቶች በማፍራት
    ስኬታማ (ፍሬያማ) መሆን የእውነት በእርግጥ ከፈለገን፤
  • 48:11 - 48:15
    ወደታች መሄድና መሠረቱን መመልከት አለብን፡፡
  • 48:15 - 48:17
    መሰረቱን መቀየር አለብን፡፡
  • 48:17 - 48:26
    አንድ ቤተክርስቲያን ባላቸው የብር መጠን ጤናማ
    ቤተክርስቲያን መሆናቸውን ማየት አትችሉም!
  • 48:26 - 48:30
    አንድ ቤተክርስቲያን ምን ያህል መልካም እንደሆነች
    ባላቸው የአባላት ቁጥር ማየት አትችሉም፡፡
  • 48:30 - 48:33
    ወይም እሁድ ምን ያህል ሰዎች እየመጡ
    ነው በሚለው ማየት አትችሉም፡፡
  • 48:33 - 48:38
    ቤተክርስቲያኒቷ ባላት የእንቅስቃሴ
    ብዛት አታዩትም፡፡ አይደለም!
  • 48:38 - 48:43
    በተለይም እሁድ እየሆነ ባለው ልታዩት አትችሉም፡፡
  • 48:43 - 48:46
    ምክንያቱም እሁድ ሁሉም ሰው እየሳቀ ነው
    ሁሉ ነገርም መልካም ይመስላል፡፡
  • 48:46 - 48:52
    አይደለም፣ የሆነ ነገር መልካም እና ጤናማ እንደሆነ
    ማየት ከፈለጋችሁ በፍሬያቸው ማየት ትችላላችሁ፡፡
  • 48:52 - 48:54
    ደቀ መዛሙርቶችን ይፈጥራሉ (ያፈራሉ)?
  • 48:54 - 49:01
    ሰዎች ኢየሱስን ያፈቅራሉ ይከተሉታል
    ቃሉንስ በድርጊትም ጭምር ይታዘዛሉ?
  • 49:01 - 49:05
    የእርሱን ቃሎች ይታዘዛሉ?
    ከኢየሱስ ጋር ስላለ ህይወት ስናወራ፣
  • 49:05 - 49:10
    አሁድ ጠዋት ብቻ አይደለም፣ ሰኞም፣
    ማክሰኞም፣ ረቡዕም፣ ሐሙስም እና ከዛም በኋላ፡፡
  • 49:10 - 49:13
    ስለዚህ አንድ ቤተክርስቲያን ጥሩ
    ቤተክርስቲያን መሆኗን ለማየት ከፈለጋችሁ፤
  • 49:13 - 49:17
    ሰዎች አርብ ምን እንደሚያደርጉ ተመልከቱ፣ ወጣት
    ሰዎች አርብ ምሽት ምን እንደሚያደርጉ ተመልከቱ፡፡
  • 49:17 - 49:20
    ጎልማሶች፣ ሽማግሌ ሰዎች ረቡዕ ከሰዓት
    ምን እንደሚያወሩ ተመልከቱ፡፡
  • 49:20 - 49:22
    ሰዎች አንድ ላይ ሲሆኑ
    ምንድን ነው የሚያደርጉት?
  • 49:22 - 49:28
    ከአፋቸው እየወጣ ያለው
    የእግዚአብሔር ቃል ኢየሱስ ነው ወይስ መጥፎ ቀልዶች?
  • 49:28 - 49:34
    ዛሬ እያደረግሁት ባለው ነገር በጣም ደፋር ነኝ
    ምክንያቱም ፍሬዎቹን አያለሁ፡፡
  • 49:34 - 49:39
    ሰዎች የኢየሱስ ደቀመዛሙርት እየሆኑ ነው፡፡
    ሰዎች እያደጉ ነው፡፡
  • 49:39 - 49:44
    እናም የዚህን ተሐድሶ ማየት እፈልጋለሁ፡፡
    አንድ ተሐድሶ ማየት እፈልጋለሁ፡፡
  • 49:44 - 49:48
    ዛሬ ብዙ ካህናትም ደግሞ ያን ተሐድሶ
    ማየት እንደሚፈልጉ አምናለሁ፡፡
  • 49:48 - 49:53
    ምክንያቱም እዚህ ቅንብር (system) ውስጥ
    እየሞቱ ያሉ ብዙ ካህናትን ተገናኝቻለሁ፡፡
  • 49:53 - 49:58
    እነርሱ ደቀ መዛሙርቶችን ማድረግ (ማፍራት) ስለፈለጉ
    ጀምረውታል፣ ነገር ግን በእሁድ ስብሰባ ተጠናቀቀ (end up)፡፡
  • 49:58 - 50:03
    እሁድ ስብሰባ፣ ረቡዕ ስብሰባ፣
    እሁድ ስብሰባ እናም ሕይወት (ኑሮ) ሄደ፡፡
  • 50:03 - 50:07
    ሰዎቹም ከዛ በኋላ እያደጉ አልነበረም
    በሆነ መልኩም እየተገደሉ ነበር፡፡
  • 50:07 - 50:13
    በባህላዊ መልኩም ደግሞ ካህን ነበርኩ
    ህይወቴም ከኔ እየወጣ ነበር፡፡
  • 50:13 - 50:19
    በእርግጥ ከባድ ነበር፡፡ አሁን ግን፣ መንገዱን
    በመቀየር በጣም ብዙ ነገሮች ተቀየሩ፡፡
  • 50:19 - 50:22
    ስለዚያ አንድ መጽሐፍ አለኝ: “የመጨረሻው ተሐድሶ”፡፡
  • 50:22 - 50:26
    ድኅረገፄ ላይ ልታዩት ትችላላችሁ፡፡
    ያን መጽሐፍ እንዲያነቡት ሰዎችን አበረታታለሁ፡፡
  • 50:26 - 50:32
    የበለጠ ትንተና ውስጥ የእውነት መሄድ ከፈለግህ
    “የመጨረሻው ተሐድሶ” መጽሐፌን አንብብ፡፡
  • 50:32 - 50:37
    በ Amazon.com ድኅረገፅ ላይ እና በሌሎች ቦታዎች
    ላይ እንደ eBook ልትገዛው (ዢው) ትችላለህ (ትችያለሽ)፡፡
  • 50:37 - 50:40
    ኤልክትሮኒክ መጽሐፉን ወይም መደበኛውን
    መጽሐፍ ልታገኙ የምትችሉበት
  • 50:40 - 50:44
    አንድ ማገናኛ (a link) በድኅረገፄ
    www.thelastreformation.com ላይ አለኝ፡፡
  • 50:44 - 50:48
    “የመጨረሻው ተሐድሶ” ን እንድታነብ አበረታታሃለሁ
    "The Last Reformation" እንድታነቢ አበረታታሻለሁ
  • 50:48 - 50:52
    ምክንያቱም ይህ በዛ ውስጥ እየወሰድኳችሁ
    እና ለምን እያደረግነው እንደሆነና
  • 50:52 - 50:55
    ምን እያደረግን እንደሆነ እያሳኋችሁ
    ያለሁት የታሪኩ አንዳንድ ክፍል ነው፡፡
  • 50:55 - 51:04
    ይህን ማለት እፈልጋለሁ: ስለዚህ ካወራችሁ፣ ችግሩ
    የቤተክርስቲያን አሠራር (ቅንብር) ብቻ አይደለም፤
  • 51:04 - 51:09
    እያደረግን ያለውን ለምንድን ነው እያደረግነው
    ያለው፡፡ ችግሩ ቲዖሎጂያችንም ጭምር ነው፡፡
  • 51:09 - 51:15
    ምክንያቱም፣ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በጣም ብዙ
    ነገሮችን ያጡበት ቲዖሎጂ እንዳላት እናያለን፡፡
  • 51:15 - 51:20
    ከዛ በእምነት መጽደቅ፣ የአማኞች ጥምቀት፣ መቀደስ፣
  • 51:20 - 51:24
    በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ እና ሌሎችም መጡ፡፡
  • 51:24 - 51:27
    እግዚአብሔር ግን እነዚያን እውነቶች
    በድጋሜ የፈጠራቸው
  • 51:27 - 51:32
    ሰዎች ከእውነቱ ጋር በየራሳቸው ሳጥን
    ውስጥ እንዲቀመጡ አይደለም፡፡
  • 51:32 - 51:35
    ዛሬ ብዙዎች፣ በተለይም እንደ
    ዴንማርክ [ባሉ] በሉተራን አገር
  • 51:35 - 51:40
    እኛ ሉተራን እንደሆንን ያምናሉ እና:
    “ኦህ፣ በሉተራን ቤተክርስቲያን ውስጥ
  • 51:40 - 51:44
    ሁሉም ነገር ስላለን መንፈስ ቅዱስ አያስፈልገንም፡፡”
  • 51:45 - 51:50
    ነገር ግን እንደዛ አይደለም ምክንያቱም
    እያንዳንዱ ነገር አንድ እውነት ነው፡፡
  • 51:50 - 51:53
    የመጨረሻው ነገር ከሁሉም የተሻለ
    ምርጥ ነው እያልኩ አይደለም፣
  • 51:53 - 51:58
    ምክንያቱም የፔንቴኮስታል ቤተክርስቲያን
    ከሜቶዲስቶች የሆነ ነገር በእርግጥ መማር ትችላለች
  • 51:58 - 52:02
    ወደ በእምነትና በቅድስና መቀደስ ሲመጣ፡፡
  • 52:02 - 52:05
    ስለዚህ ይህ ምርጡ ነው አልልም፡፡
    አልልም፡፡
  • 52:05 - 52:11
    እያንዳንዱ እውነት አንድ ላይ ሆኖ
    ሲመጣ ልናየው እንዳለ አምናለሁ፡፡
  • 52:11 - 52:15
    ነገር ግን እነኚህ ትልልቅ የእምነት
    ወገኖች በአንድ ላይ ሆነው አንድ በመሆን
  • 52:15 - 52:20
    ወደ አንድነት አይመጣም፡፡ አይመጣም፣
    ምክንያቱም ያን ማድረግ አትችሉም፡፡
  • 52:20 - 52:25
    ብዙ ቤተክርስቲያኖች በድጋሜ ወደ
    ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እያዘነበሉ ያሉበት
  • 52:25 - 52:28
    የሐሰት መነቃቃት ሲሆን ዛሬ [ላይ] እያየን ነው፡፡
  • 52:28 - 52:31
    የፔንቴኮስታል ካህናት እንዴት ወደ
    ካቶሊክ ቤተክርስቲያን
  • 52:31 - 52:33
    ለማዘንበል መጀመራቸው አስደንግጦኛል፡፡
  • 52:33 - 52:37
    የቤተክርስቲያን አባቶች ብለው ይጠሩታል፡፡
  • 52:37 - 52:40
    ወደ እነዚያ ባህሎች አትመለሱ…
    በዚህ ፈንታ ወደ ሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ፣
  • 52:40 - 52:43
    ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ተመለሱ፡፡
  • 52:43 - 52:46
    እነርሱ ግን ወደ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እያዘነበሉ ነው
  • 52:46 - 52:49
    ይህም አሁን ሲሆን እያየነው ያለው
    ሐሰተኛው መነቃቃት ነው፡፡
  • 52:49 - 52:53
    ጠብቁ ብቻ፣ በቅርቡ ወደፊት በጣም የበለጠ፣
    የበለጠ ሊሆን ነው፡፡
  • 52:53 - 52:57
    ነገር ግን እውነተኛው መነቃቃት
    ሰዎች ከእነዚያ ውስጥ ሊወጡ ነው፡፡
  • 52:57 - 53:00
    ሳጥኖቹም ሊወድቁ ነው፡፡
  • 53:00 - 53:03
    ከዚያም እኛ እንደ አንድ ሕዝብ (ሰዎች) ልንተባበር ነው፡፡
  • 53:03 - 53:07
    በጎዳና ላይ እና በቤታቸው ውስጥ
    ከሰዎች ጋር ከተገናኛችሁ
  • 53:07 - 53:12
    ግንባራቸው ላይ ምንም የለም--
    ፔንቴኮስታል ወይም መጥምቃውያን፡፡ አይደለም!
  • 53:12 - 53:17
    አንተ የእውነት የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነህ እናም እግዚአብሔር
    እንድናደርገው የሚፈልገው ይህ ነው ብዬ አምናለሁ:
  • 53:17 - 53:22
    መማር እንድንችልና ሁሉን ነገር ትክክል እንድናደርግ
    እኛን እንደ አንድ ሕዝብ ማቀናጀት፡፡
  • 53:22 - 53:25
    ምክንያቱም አንድ እውነት ሊኖራችሁ ስለምትችሉ፡፡
  • 53:25 - 53:30
    ነገር ግን ያ እውነት ብቻ ቢኖራችሁና ሌላኛው
    እውነት ባይኖራችሁ፤ ስህተተኞች ናችሁ፡፡
  • 53:30 - 53:38
    አዎ፣ አንተ በእምነት ጸድቀሃል፣ ነገር ግን
    ኢየሱስ ሰዎችን ማጽደቅ አላለም፡፡
  • 53:38 - 53:46
    አይደለም፣ እርሱ ያለው ሰዎች ይታዘዙኝ ዘንድ ውጡና
    ሰዎችን ደቀ መዛሙርቴ እንዲሆኑ አድርጓቸው፡፡
  • 53:46 - 53:52
    እርሱን ለመታዘዝም አሮጌውን ህይወት መቅበር
    አለብን ደግሞም ቅዱስ ህይወት ልንኖር ያስፈልገናል፡፡
  • 53:52 - 53:57
    የዘላለም ሕይወት ላይ ልናተኩር ያስፈልገናል፣
    መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገናል፣
  • 53:57 - 54:06
    ስጦታዎቹ ያስፈልጉናል፣ የኢየሱስ ተከታይና
    ደቀ መዝሙር ወደ መሆን ሲመጣ፡፡
  • 54:06 - 54:14
    ላሳያችሁ ብቻ እፈልጋለሁ፣ የቲዖሎጂ ምሳሌ
    ለመውሰድ፣ እንዴት መጥፎ ነው፡፡
  • 54:14 - 54:23
    አስር አመት የሆናቸው አስር ሕፃናት ብወስድ
    እኔም አንድ መጽሐፍ ቅዱስ ብሰጣቸው፡፡
  • 54:23 - 54:27
    እኔም ወንጌላትንና የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን
    እንዲያነቡ እነዚያን አስር ሕፃናት ብጠይቃቸው፡፡
  • 54:27 - 54:31
    ከዛም አንድ ሰው መቼ ነው የሚጠመቀው
    ብዬ ጠየቅኳቸው?
  • 54:32 - 54:38
    ወደ እምነት ከመጣ በኋላ የመጀመሪያው
    እሁድ [ዕለት] ነው? ከሆኑ ወራት በኋላ?
  • 54:38 - 54:41
    በቤተክርስቲያን ውስጥ አንዳንድ ትምህርት እንደተቀበሉ?
  • 54:41 - 54:46
    ወይስ ከብዙ ዓመታት በኋላ ለመጠመቅ
    ዝግጁ እንደሆኑ ሲሰማቸው?
  • 54:46 - 54:51
    ሕፃናቱ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን
    ካነበቡ ይመለከቱኝና እንዲህ ይላሉ:
  • 54:51 - 54:55
    ከእነዚህ አንዳቸውም አይደለም፣ ነገር ግን
    ወዲያውኑ [ያመኑ] ያንኑ ቀን፣ ለምን?
  • 54:55 - 55:01
    ምክንያቱም ይህ በጣም ግልፅ ነው፣ በጣም ግልፅ ከመሆኑ
    የተነሣ የአስር ዓመት ሕፃናት [እንኳ] ሊያዩት ይችላሉ:
  • 55:01 - 55:06
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ወደ እምነት
    የመጣ እያንዳንዱ ሰው ያንኑ ቀን ተጠምቋል፡፡
  • 55:06 - 55:12
    እያንዳንዱ ሰው ንስሐ ገባ እናም ተጠመቀ
    እና መንፈስ ቅዱስን ተቀበለ፡፡
  • 55:12 - 55:18
    መጀመሪያው ነበረ እና ለአስሩ
    ሕፃናት በጣም ግልፅ ነበረ፡፡
  • 55:19 - 55:29
    ነገር ግን ከእያንዳንዱ የእምነት ወገን
    አምስት በጣም ንቁ ሰዎችን ብወስድ፣
  • 55:29 - 55:33
    ግሪክ እና ዕብራይስጥ ማንበብ የሚችሉ፣
  • 55:33 - 55:40
    እና ለብዙ ዓመታት ቲዖሎጂ ሲያጠኑ
    የነበሩ እና ያንኑ ጥያቄ ብጠይቃቸው:
  • 55:40 - 55:43
    “አንድ ሰው መቼ ነው የሚጠመቀው?”
  • 55:43 - 55:47
    እነርሱ አምስት የተለያዩ መልሶች ይሰጡኛል፡፡
  • 55:47 - 55:50
    የት ነው ሲያጠኑ የነበረው የሚለው ይወስነዋል፡፡
  • 55:50 - 55:55
    ከመልሶቹ አንዳቸውም እውነቱ አይደሉም፡፡
  • 55:55 - 55:58
    ሰዎችን ያንኑ ቀን ማጥመቅ?
    አንዳቸውም፡፡ ለምን?
  • 55:58 - 56:00
    ምክንያቱም ይህ የእነርሱ ሳጥኖቻቸው
    ውስጥ አይገባም (አይገጥምም)፡፡
  • 56:00 - 56:05
    ከሃይማኖታችን የተነሣ የእግዚአብሔርን ቃል በሆነ
    መልኩ ከኃይል ውጪ አድርገን ወስደነዋል፣
  • 56:05 - 56:07
    ከባህሎቻችን የተነሣ፡፡
  • 56:07 - 56:11
    ምክንያቱም ሰዎችን [በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ባመኑበት]
    በዚያው ቀን ማጥመቃችን
  • 56:11 - 56:13
    በዚህ የቤተክርስቲያን ወገን ሳጥን ውስጥ አይገጥምም፡፡
  • 56:13 - 56:16
    ምክንያቱም እኛ የምንፈልገው ቤተክርስቲያን
    ውስጥ እንዲሆን ነው፣ ስብሰባ ላይ፣
  • 56:16 - 56:18
    የተቀናጀም [ደግሞ] መሆን አለበት፡፡
  • 56:18 - 56:22
    በዚያ ምክንያት ኃይሉን እያጣን ነው
    ሕይወቱንም እያጣን ነው፡፡
  • 56:22 - 56:27
    ምክንያቱም እግዚአብሔር ባህሎቻችንን አያጸናም፣
    እርሱ የራሱን ቃል ነው የሚያጸናው፡፡
  • 56:27 - 56:30
    ሰዎች [በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ባመኑ] በዚያው ቀን
    ማጥመቅን-ተለማምጃለሁ [አጥምቄአለሁ]፣
  • 56:30 - 56:33
    በዚያም መንፈስ ቅዱስ እየወረደ
    ስለነበር በዙሪያ [በአካባቢው] ያሉ ሰዎች
  • 56:33 - 56:37
    ማንም ሰው ሳይጸልይላቸው ወዲያውኑ
    በልሳኖች መናገር ጀምረው ነበር፡፡ ለምን?
  • 56:37 - 56:40
    ምክንያቱም እግዚአብሔር ይህን ወዶታል!
    እግዚአብሔር ቃሉን ያፈቅራል!
  • 56:40 - 56:44
    እኛ እርሱን ስንታዘዘውና ስናከብረው እንዲሁም እርሱ
    እንድናደርገው የጠራንን ስናደርግ እግዚአብሔር ይህን ይወዳል፡፡
  • 56:44 - 56:47
    ባህሎቻችን እንድናደርገው
    የነገሩንን አይደለም [የምናደርገው]፡፡
  • 56:47 - 56:52
    ስለዚህ አያችሁ ግሪክና ዕብራይስጥ
    የሚችሉ እነዛ ትልልቅ ጎበዝ ሰዎች፣
  • 56:52 - 56:58
    ቃሉ እያለ ያለውን ማየት አይችሉም፡፡
    አስር ሕፃናት ግን ሊያዩት ይችላሉ፡፡
  • 56:58 - 57:04
    ሁሉም ስለባህሎች እንደሆነ፣ ወይም ሁሉም ስለ እውቀት፣
    ሁሉም ስለ ትምህርት እንደሆነ በተደጋጋሚ ብዙ ጊዜያት አምነናል፡፡
  • 57:04 - 57:05
    በተደጋጋሚ ብዙ ጊዜያት አምነናል፡፡
  • 57:05 - 57:10
    ዛሬ በዓለም ዙሪያ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ብዙ
    ሰዎች እኔ ማምለክ ከፈለግሁ ወይም እግዚአብሔርን
  • 57:10 - 57:19
    ማገልገል ከፈለግሁ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት በቃ
    መሄድ አለብኝ ብለው ያስባሉ፡፡ ስህተት! ሐቀኛ ለመሆን፣ ስህተት!
  • 57:19 - 57:25
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ፣ እነርሱ የመጽሐፍ ቅደስ ትምህርት
    ቤት ሄደው ነበር? አልሄዱም! ኢየሱስን ያውቁ ነበር? አዎ
  • 57:25 - 57:29
    በጣም ብዙ እውቀት ነበራቸው? አዎ፡፡ ነገር ግን ከኢየሱስ ጋር
    አንድ ላይ በመሆን ነበር ይህን ያገኙት፣
  • 57:29 - 57:31
    በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት
    ውስጥ በማጥናት አልነበረም፡፡
  • 57:31 - 57:36
    የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት በግድ ስህተት ነው አላልኩም
    ነገር ግን ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ጋር ያለው ስህተት
  • 57:36 - 57:39
    አንተ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ስትጨርስ፣
  • 57:39 - 57:42
    መጽሐፍ ቅዱስን በተለያዩ መነጽሮች ታነባለህ፡፡
  • 57:42 - 57:48
    ለምሳሌ፣ ቲዖሎጂ ሲያጠና የነበረ አንድ
    ሰው ብገናኝ [ገና] ከእርሱ ጋር ሳልነጋገር
  • 57:48 - 57:51
    ይህ ሰው ምን እንደሚያምን ልነግራችሁ እችላለሁ፡፡
  • 57:51 - 57:54
    እርሱ የት ሲያጠና እንደነበር ብቻ ነው
    ማወቅ ያለብኝ፡፡
  • 57:54 - 57:58
    በሉተራን ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያጠና ከነበረ:
    “ኦህ፣ አንተ ይህን እና ይህን ታምናለህ..”
  • 57:58 - 58:00
    በሜቶዲስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያጠና
    ከነበረ “አንተ ይህን እና ይህን ታምናለህ፡፡ ”
  • 58:00 - 58:05
    በመጥምቃውያን ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያጠና ከነበረ:
    “አንተ በዚህ እና በዚህ ታምናለህ”፡፡ ማየት ቻላችሁ? አያችሁት?
  • 58:05 - 58:13
    በሆነ መልኩ እንዲህ ነው:
    ስንድን ወይም ስንቧደን፣
  • 58:13 - 58:16
    በአንድ ቤተክርስቲያን ወገን ውስጥ፣ በአንድ ቤተክርስቲያን
    ቅንብር ውስጥ እንድናለን ወይም እንቧደናለን፡፡
  • 58:16 - 58:23
    በተደጋጋሚ ብዙ ጊዜም፣ ያደግንበት ቤተክርስቲያን
    ብቸኛው እውነት ነው ብለን እናምናለን፡፡ ወይም የጀመርንበት፡፡
  • 58:23 - 58:29
    ምክንያቱም የምናየው ነገር ሁሉ እያደረግነው
    ያለው ነገር እውነቱ እንደሆነ ይመስላል፡፡
  • 58:29 - 58:34
    መጽሐፍ ቅዱስን ከእኛ በጣም በተሻለ
    የሚያውቁ ንቁ (ጎበዝ) ሰዎች በዙሪያችን አሉን፡፡
  • 58:34 - 58:36
    ስለዚህ በዚያ ምክንያት [እያደረግነው ያለው ነገር]
    እውነቱ መሆን አለበት፡፡
  • 58:36 - 58:39
    ነገር ግን ሁሉም ሰው በዙሪያው መጽሐፍ ቅዱስን
    የሚያውቁ ንቁ (ጎበዝ) ሰዎች እንዳሉት ረስተናል፡፡
  • 58:39 - 58:44
    ሁሉ ሰውም እያደረጉት (እያደረግሁት)
    ያለው ነገር እውነቱ ነው ብሎ ያምናል፡፡
  • 58:44 - 58:49
    በተደጋጋሚ ግን ማየት አንችልም፡፡ ምክንያቱም የምናነበው
    በእነዚህ መነጽሮች ውስጥ (በኩል) ስለሆነ፡፡
  • 58:49 - 58:56
    በብዙ መልኮች በጣም ንቁ (ጎበዝ) የሆኑ በሉተራን አገልግሎት
    ውስጥ ካህናት የሆኑ ጓደኞች እኔም አሉኝ፣
  • 58:56 - 59:00
    ወደ ጥምቀት ሲመጣ (ጥምቀትን አስመልክቶ)
    ግን ማየት አልቻሉም፡፡
  • 59:00 - 59:05
    እነርሱ እያሉ ያሉትን ሳነብ… እነርሱ አንድ ሥራ ያለባቸው
    ትምህርት ቤት ውስጥ አስተማሪ ብሆን ኖሮ፣
  • 59:05 - 59:12
    ዝቅተኛውን ውጤት እሰጣቸው ነበር፡፡
    ለምን?
  • 59:12 - 59:16
    ምክንያቱም [እያሉ ያሉት ነገር] በጣም
    መጥፎ ነው፣ ወደ ቲዖሎጂያቸው ሲመጣ፡፡
  • 59:16 - 59:20
    በብዙ ሌሎች መንገዶች እነርሱ ጠንካራ ናቸው፣
    ነገር ግን ወደዛ ሲመጣ በጣም መጥፎ ነው፡፡
  • 59:20 - 59:25
    ከመነፅሮቻቸው የተነሣ ሊያዩት አልቻሉም፡፡
    ወይም እነርሱ ለማየት ፈርተዋል፡፡
  • 59:25 - 59:32
    ምክንያቱም በድንገት ካዩት፣ እና
    በጥምቀት ላይ ዕይታቸውን ከቀየሩ፣ ለምሳሌ፣
  • 59:32 - 59:36
    ከዚያ እነርሱ ሥራቸውን፣ ጓደኞቻቸውንና
    ገንዘባቸውን ሊያጡ ነው፡፡
  • 59:36 - 59:42
    ከእንግዲህ ሳጥኑ ውስጥ ስላልሆኑ
    እነርሱ ሁሉንም ነገር ሊያጡ ነው፡፡
  • 59:42 - 59:46
    ችግሩ ይህ ነው፣ ትክክለኛውን ቲዖሎጂ
    እንዳናገኝና እግዚአብሔርን እንዳናውቅ
  • 59:46 - 59:51
    በተደጋጋሚ ያስተጓጉሉናል፡፡
    ሳጥኖቻችን! ሳጥኖቻችን!
  • 59:51 - 59:55
    ከሳጥኑ ጋር ችግር ባይኖር ኖሮ፣ ምን ያህል
    ብዙ ጊዜ በተደጋጋሚ፣ ሁል ጊዜ እናይ ነበር፣
  • 59:55 - 59:59
    መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነብ አንድ ካህን:
    “ሄይ፣ አጥማቂ(መጥምቃዊ) ሆንኩ!”
  • 59:59 - 60:03
    ወይም ስለ መንፈስ ቅዱስ የሚያነብ አንድ
    መጥምቃዊ: “ኦህ፣ ፔንቴኮስታል ሆንኩ፡፡”
  • 60:03 - 60:06
    ነገር ግን ምን ያህል በተደጋጋሚ ነው ያን የምናየው?
    በጣም በተደጋጋሚ (ብዙ ጊዜ) አይደለም፡፡
  • 60:06 - 60:11
    አብዛኛውን ጊዜ፣ ድናችሁ የገባችሁበት
    የቤተክርስቲያን ቅንብር (አሠራር)፡፡
  • 60:11 - 60:17
    ያደጋችሁበት [አሠራር] በሕይወታችሁ
    ዘመን በሙሉ በዚያው ትቀጥላላችሁ፡፡
  • 60:17 - 60:23
    እውነቱና እውነቱ ብቻ ያላት በትክክለኛዋ
    ቤተክርስቲያን ወገን ውስጥ ስላደጋችሁ
  • 60:23 - 60:26
    በጣም እድለኛ እንደሆናችሁ ታምናላችሁም፡፡
  • 60:26 - 60:29
    ማንኛውም [ሰው] ብቻውን እውነቱ ብቻ
    አለው ብዬ አላምንም፡፡
  • 60:29 - 60:34
    መላውን እውነት ማግኘት ከመቻላችን በፊት ከእያንዳንዳቸው
    [የቤተክርስቲያን ወገኖች] ከእውነቱ አንዳንዱን
  • 60:34 - 60:36
    ማግኘት አለብን ብዬ አምናለሁ፡፡
  • 60:36 - 60:40
    ስለዚህ፣ ስለ ቲዖሎጂ ብቻ አይደለም ለማለት እፈልጋለሁ፡፡
  • 60:40 - 60:43
    መነጽሮቹን ከአንተ (ከአንቺ) ላይ በእርግጥ
    የእውነት ስለማውለቅ ነው፡፡
  • 60:43 - 60:47
    ከሰዎች ጋር ቲዖሎጂ መነጋገር (መወያየት)
    አልፈልግም፣ ያን በፊት (ድሮ) አድርጌዋለሁ፡፡
  • 60:47 - 60:50
    በንግግሮች (በውይይቶች) በጣም ብዙ
    ጊዜ ማባከን አልፈልግም፡፡
  • 60:50 - 60:54
    ለማሰልጠንና እንደዚህ ዓይነት ትምህርት
    ለማድረግ ሰዓቱን መጠቀም እፈልጋለሁ፣
  • 60:54 - 60:59
    ስለዚህ ሰዎች መነፅሮቻቸውን ከላያቸው ላይ ማውለቅ
    ይችላሉ፣ እናም መንፈስ ቅዱስ እያስተማራቸው
  • 60:59 - 61:02
    ለራሳቸው መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ይጀምራሉ፡፡
  • 61:02 - 61:07
    ያን ስታደርግ፣ በድንገት አንተ: “ዋው፣
    ከዚህ በፊት ያላየሃቸውን ነገሮች ታያለህ፡፡
  • 61:07 - 61:12
    ዌብሳይቴ ለምን “የመጨረሻው ተሐድሶ”
    ተብሎ አንደተጠራ አሁን አውቀሃል፡፡
  • 61:12 - 61:16
    እዚህ አለኝ: የካቶሊክ ሲስተም (ቅንብር፣ አሠራር)
    መውደቅ አለበት እና
  • 61:16 - 61:20
    ኢየሱስ ተመልሶ ከመምጣቱ በፊት እግዚአብሔር
    ሁላችንንም በአንድ ላይ አምጥቶናል፡፡
  • 61:20 - 61:26
    “የመጨረሻው ተሐድሶ”፣
    ያም የመጽሐፌና የዌብሳይቴ ስም ነው፡፡
  • 61:26 - 61:30
    አንተ እዚህ የተቀበልከው
    ከትምህርቱ አንዳንዱን ነው፡፡
  • 61:30 - 61:34
    ከመጨረሻው ተሐድሶ ፊት ለፊት
    እንደቆምን አምናለሁ ምክንያቱም
  • 61:34 - 61:39
    እግዚአብሔር ከፊት ለፊታችን፣ ላለፉት ብዙ ዓመታት፣
    የራሱን ቤተክርስቲያን እየገበና ነበር እና
  • 61:39 - 61:42
    እርሱ (እግዚአብሔር) መነፅሮቻችንን
    ከላያችን ላይ እንድናወልቅ ይፈልጋል፡፡
  • 61:42 - 61:47
    ከተሳሳተ መሰረታችን ውስጥ ሰብረን እንድንወጣና
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ ወዳነበብነው
  • 61:47 - 61:52
    ወደ ቀላሉ፣ ነገር ግን ኃይለኛ [ወደሆነው] ሕይወት
    ተመልሰን እንድንመጣ እርሱ ይፈልጋል፡፡
  • 61:52 - 61:57
    ህሙማንን መፈወስ ለመማር ፈልገው
    ልክ ከሆላንድ እንደመጡት ሰዎች
  • 61:57 - 62:04
    በጣም ብዙ ትምህርት አልሰጠኋቸውም
    ነበር ትንሽ ቡና ጠጣን፣ ስለ ኢየሱስ
  • 62:04 - 62:09
    እና ስለ ብዙ የተለያዩ ነገሮች አወራን
    ከዚያም ለሌሎች ሰዎች እንዳደረግኩት
  • 62:09 - 62:10
    ወደ ጎዳናዎች ወሰድኋቸው፡፡
  • 62:10 - 62:16
    በሃያ ደቂቃዎች ውስጥም ለታመሙ
    ሰዎች ጸለዩ ሰዎቹም ተፈወሱ፡፡
  • 62:19 - 62:27
    በጣም ብዙ ትምህርት አልይዝም፡፡ አልይዝም፣
    ምክንያቱም ሕይወቱን ካሳየናቸው
  • 62:27 - 62:32
    እና ኢየሱስ ባደረገበት መልኩ ካሰለጠንናቸው፣
    በጣም ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡
  • 62:32 - 62:35
    እናም ይህን ነው በዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት
    ቤት ጊዜ ከእናንተ ጋር ማድረግ የምፈልገው፡፡
  • 62:35 - 62:42
    በቀጣዮቹ 19 ትምህርቶች
    በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ
  • 62:42 - 62:45
    ወዳነበባችሁት ሕይወት ቀስ በቀስ
    ወደኋላ እወስዳችኋለሁ፡፡
  • 62:45 - 62:48
    “ስለዚህስ? እና ምን ማድረግ አለብን?
    እና… ይህስ?” አይነት
  • 62:48 - 62:50
    ብዙ ጥያቄዎች እንደሚኖሩ አውቃለሁ፡፡
  • 62:50 - 62:56
    ይህን እላለሁ: ተረጋጉ፣ በአንድ ጊዜ አንድ
    እርምጃ፣ ያን በኋላ ላይ ትረዱታላችሁ፡፡
  • 62:56 - 63:02
    አሁን እንድታደርጉት የምፈልገው ግን፣ በሚቀጥለው
    ሳምንት ከእናንተ ጋር ቀጣዩን ትምህርት ከማድረጌ በፊት፣
  • 63:02 - 63:07
    መጽሐፍ ቅዱስን፣ የሐዋርያት ሥራ
    መጽሐፍን እንድትወስዱ እፈልጋለሁ፡፡
  • 63:07 - 63:13
    ከመጀመሪያው ጀምራችሁ የሐዋርያት
    ሥራ መጽሐፍን ማንበብ ጀምሩ በቃ፡፡
  • 63:13 - 63:17
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን ስታነቡ
    በውስጡ ቤተክርስቲያንን ታያላችሁ፡፡
  • 63:17 - 63:21
    ከዚያ ለራስህ እንዲህ በል: “ይህ ኖርማል
    (ትክክለኛ፣ መደበኛ) የክርስቲያን ሕይወት ነው!”
  • 63:22 - 63:28
    “ይህ ኖርማሉ (ትክክለኛው፣ መደበኛው) የክርስቲያን ሕይወት
    ነው!” የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን አንብብ (አንብቢ)፡፡
  • 63:28 - 63:32
    ለራስህም “ይህ ኖርማሉ (ትክክለኛው፣ መደበኛው)
    የክርስቲያን ሕይወት ነው!” ብለህ ንገረው፡፡
  • 63:32 - 63:41
    ያለህበትን ቅንብር (ድባብ) ለመርሳት ሞክር፣
    በዙሪያሽ የምታዪውን ለመርሳት ሞክሪ፡፡
  • 63:41 - 63:47
    ይህ መደበኛ ነው ብለሽ አታስቢ፡፡
    የእግዚአብሔር ቃል፣
  • 63:47 - 63:50
    የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ነው መደበኛ
    (ትክክለኛ) የክርስቲያን ሕይወት፡፡
  • 63:50 - 63:54
    ስለዚህ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍን ውሰድና
    እስከመጨረሻው አንብበው፡፡ የበለጠ ከፈለግህም፣
  • 63:54 - 63:57
    መጽሐፌን “የመጨረሻው ተሐድሶ” እዘዝ፡፡
    በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት እየተማርክ ሳለ
  • 63:57 - 64:01
    ያ [መጽሐፍ] ካለህና እስከመጨረሻው
    ካነበብከው ጥሩ (መልካም) ይሆናል፡፡
  • 64:01 - 64:06
    በጣም ትልቅ በረከት ሊሆንልህ ይችላል፡፡
    በተረፈ በቀጣዩ ሳምንት ላያችሁ እፈልጋለሁ፡፡
  • 64:06 - 64:10
    ያን ቀን እጠብቃለሁ፡፡ በሚቀጥለው ሳምንት
    የማወራውና የማወጣው፡፡
  • 64:10 - 64:14
    በጥቂቱ ጨምሬ ስለ ሲስተሙ (ስለ ደምቡ፣ ስለ አሠራሩ)
    አወራለሁ አብራራለሁም፡፡
  • 64:14 - 64:17
    ስለ ክህነት፣ ሁላችንም ካህናት ስለመሆናችን፡፡
  • 64:17 - 64:23
    በህይወትህ ውስጥ ልታድግበት የምትችልበት አንድ
    መምሪያ (መድረክ) ለመፍጠርም ረዳሃለሁ፡፡
  • 64:23 - 64:26
    ምክንያቱም ዛሬ በምዕራቡ ሁሉም ነገር
  • 64:26 - 64:31
    ስለ እውቀት የሆነ ክርስትና ገንብተናል፡፡
  • 64:31 - 64:36
    ነገር ግን ነገር ሁሉ ስለ እውቀት አይደለም፣
    አውቆ ስለማድረግ (ስለማወቅና ስለማድረግ) ነው፡፡
  • 64:36 - 64:41
    በተደጋጋሚ ይህን እናስባለን: “ኦህ፣ ተጨማሪ ቲዖሎጂ
    ያስፈልገኛል፣ የበለጠ የመጽሐፍ ቅደስ ትምህርት ቤት፣
  • 64:41 - 64:43
    ተጨማሪ እውቀት ያስፈልገኛል፡፡”
  • 64:43 - 64:47
    ነገር ግን ቲዖሎጂን ለብዙ ዓመታት
    ሲያጠኑ የነበሩትን ሰዎች ብትመለከቱ፡፡
  • 64:47 - 64:53
    የበለጠ ባጠኑ ቁጥር፣ በእግዚአብሔር
    መንግሥት ውስጥ ዝቅተኛ ጠቃሚ ናቸው
  • 64:53 - 64:57
    እድገትን ወደማየት፣ ጋኔንን ወደ ማስወጣት፣ ህሙማንን ወደ
    መፈወስ ሲመጣ፣ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ዝቅተኛ ጠቃሚ ናቸው
  • 64:57 - 65:00
    ከእግዚአብሔር መስማትና በመንፈስ ቅዱስ ስለመመራት ሲመጣ
    በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ዝቅተኛ ጠቃሚ ናቸው፡፡
  • 65:00 - 65:06
    ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ቃል በተግባርና በቀላሉ
  • 65:06 - 65:08
    በመታዘዝ ፈንታ ቲዖሎጂ መጣ፡፡
  • 65:08 - 65:12
    ከሆላንድ ከመጡት ጥንዶች ጋር ያደረግሁት
  • 65:12 - 65:22
    የእነርሱን ህይወት ከማደስና ሙሉ በሙሉ ከመቀየር አንፃር
    በጣም አክራሪ ነበር፣ 20 ደቂቃዎች ብቻ ወሰደ፡፡
  • 65:23 - 65:28
    ከእነርሱ ጋር አወራሁና እንዲህ አልኳቸው
    ይህ በጣም አስገራሚ ነው በጣምም ቀላል ነው፣
  • 65:28 - 65:30
    ምንም አዲስ ነገር የለም፣ ኢየሱስ
    በሉቃስ 10፡9 ላይ ያለውን ብቻ ነው ያደረግነው፡፡
  • 65:30 - 65:33
    ወደ ውጭ ሂዱ፣ ድውዮችን ፈውሱና ወንጌልን
    (የምሥራቹን) ስበኩ፡፡ “እሺ፣ እናድርገው፡፡”
  • 65:33 - 65:39
    ነገር ግን ነገሮችን በማድረግ ፈንታ
    በተደጋጋሚ ከነገሮች ውስጥ ቲዖሎጂ እንገነባለን፡፡
  • 65:39 - 65:42
    ለእኔና ለአንተ ግን ለማድረግ፣ አንድ
    መምሪያ (መድረክ) ያስፈልገናል፣
  • 65:42 - 65:46
    ኢየሱስ የየዕለት ህይወታችን ውስጥ አካል መሆን
    እንደሚፈልግ ልንረዳ ያስፈልገናል፡፡
  • 65:46 - 65:49
    አዎ፣ እኔም ስለዛ በሚቀጥለው ሳምንት እናገራለሁ፡፡
  • 65:49 - 65:52
    እግዚአብሔር ይባርካችሁ
    በሚቀጥለው ሳምንትም እንገናኝ፡፡ ደህና ሁኑ፡፡
Title:
ትምህርት 1 - ከሳጥኑ ውስጥ ውጡ - ፋና ወጊው ትምህርት ቤት
Description:

http://www.TheLastReformation.com
ከሳጥኑ ውስጥ ውጣ፡፡ ዛሬ የምናደርጋቸው አብዛኛዎቹ ነገሮች በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ምክንያት ነው፡፡ መነፅራችንን ለማውለቅ ይህን መረዳት ጠቃሚ (አስፈላጊ) ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል እንዳለውኑ እንዳናነብ የሚያስታጉሉን እነዚያ፡፡ ይህ በጣም ጠቃሚ ትምህርት ነው ቶርበን በፋና ወጊው ትምህርት ቤት ጊዜ ወደዚህ ደግሞ ደጋግሞ ተመልሶ ይመጣል ፡፡

more » « less
Video Language:
English
Duration:
01:05:53

Amharic subtitles

Revisions